በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት

Public Relation

A message transmitted by Hisgrace Abune Gerima Bishop

​A message transmitted by His Eminence Abune Gerima, bishop of the Gedeo, Kore, and Burji Diocese and Member of the Holy Synod, regarding the 2018 E.C. Nativity of Our Lord and Savior Jesus Christ, addressed to his spiritual children within the Gedeo, Kore, and Burji Diocese, across the nation, and in various parts of the world. ​Ichthus: Tahsas 28, 2018 E.C.

A message transmitted by Hisgrace Abune Gerima Bishop Read More »

Eebbisemeek Abune Geriima Gede’o Koorenna Burjixxe Hagere Sibkete Phaaphaasichchi Qullitte Sinoodeesexxi una 2018 G.W Goottanna Qorsa Iyyesuusi Kiristoosika ilenshatika ayyaana uuddaaxxin Qullichchi manfasixxe ila insa’nexxee Gede’uffat Laagadinni Sa’issineexxa erga.

Ekituus Arfaasa 28/2018 G.W

Eebbisemeek Abune Geriima Gede’o Koorenna Burjixxe Hagere Sibkete Phaaphaasichchi Qullitte Sinoodeesexxi una 2018 G.W Goottanna Qorsa Iyyesuusi Kiristoosika ilenshatika ayyaana uuddaaxxin Qullichchi manfasixxe ila insa’nexxee Gede’uffat Laagadinni Sa’issineexxa erga. Read More »

ብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል የ2018 ዓ.ም የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓልን በተመለከተ በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት፣ በሀገር ውስጥና በተለያዩ ክፍላተ ዓለም ለሚገኙ ለመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቸው ያስተላለፉት መልእክት።

ኤክቱስ ታኅሣሥ 28/2018 ዓ.ም

ብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል የ2018 ዓ.ም የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓልን በተመለከተ በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት፣ በሀገር ውስጥና በተለያዩ ክፍላተ ዓለም ለሚገኙ ለመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቸው ያስተላለፉት መልእክት። Read More »

ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ልደቱ ለእግዚእነ ወአምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ  ዘዕሥራ ምእት ዓሠርቱ ወሰምንቱ ዓመት ምሕረት

ኤክቱስ ታኅሣሥ 28/2018 ዓ.ም በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! +  በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፣+  ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፣+  የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፣+  በሕመም ምክንያት በየፀበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፣+  እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያት በሙሉ፣ እኛ በሕይወት እንኖር ዘንድ አንድ ልጁን ወደ ዓለም የላከ እግዚአብሔር ኣምላካችን እንኳን ለሁለት ሺሕ ዓስራ ስምንት ዓመተ ምሕረት በዓለ ልደቱ በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ!“ወበዝንቱ ተዓውቀ ፍቅሩ ለእግዚአብሔር ላዕሌነ እስመ ለወልዱ ዋሕድ ፈነዎ ውስተ ዓለም ከመ ንሕየው በእንቲኣሁ፤ ወዝንቱ ውእቱ ፍቅሩ ለእግዚአብሔር፡- የእግዚአብሔር ፍቅሩ በእኛ ዘንድ ተገለጠ፤ በእርሱ በኩል በሕይወት እንኖር ዘንድ እግዚአብሔር አንድ ልጁን ወደ ዓለም ልኮታልና የእግዚአብሔር ፍቅር ይህ ነው፤ (፩ዮሓ. ፬፥፱) በሁሉም ዘንድ እንደሚታወቀው እኛ ምሥራቃውያን ክርስቲያኖች በዛሬው ዕለት የምናከብረው በዓል፣ የጌታችን የኣምላካችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት ነው፤ በዓለ ልደት የእግዚአብሔር ሰላምና ፍቅር ለሰው ልጆች ሁሉ የታወጀበት ዕለት ነው፤ በዚህ ዕለት የሆነው የእግዚአብሔር ፍቅርና ሰላም ቃላዊ ወይም ተምኔታዊ ኣልነበረም፤ ወይም ደግሞ በርቀት በመልእክት የተላለፈ ኣልነበረም፤ከዚህ ይልቅ ሰብእናችንን በመዋሐድ፣ በተግባር ሆኖ በመገኘት፣ እንዲሁም ለመሰጠት ዝግጁ በመሆን የተገለጠና የታየ ሰላምና ፍቅር ነው፤ እግዚአብሔር የኛን ሰላምና ፍቅር በእጅጉ የሚሻው መሆኑን ለመረዳት፣ የኛን ሰብአዊ ክዋኔ በምልአት ተዋሕዶ በመካከላችን ከመገኘት የተሻለ ሌላ ማረጋገጫ ሊኖር ኣይችልም፤ እኛ ሰዎች ለእግዚአብሔር ጠላቶቹ ተብለን በቅዱስ መጽሐፍ የተገለጽን ነን:: እግዚአብሔር ጠላቶቹን የራሱ አካል አደረጋቸው ሲባል ከመስማት የበለጠ አስደናቂ ነገር በዚህ ዓለም ምን ሊኖር ይችላል? የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት! እግዚአብሔር ሰብኣዊነታችንን በምልአት ተዋሕዶ በዓለማችን እንዲገለጥ የሆነበት ዋና ምክንያት እሱ እንዳስረዳን እኛ በሕይወት እንድንኖር ነው፤ ይህንንም ያደረገው ከሁሉ በላይ የሆነ ሌላ ገፊ ኃይል ገፋፍቶት ሳይሆን ድንበር የለሽና ፍጹም ፍቅሩ አነሣሥቶት እንደሆነ ከቅዱሳት መጻሕፍት እንረዳለን፤ የእግዚአብሔር ፍቅር እኛ ከምናውቀው ፍቅር ሁሉ በላይ መሆኑንም በዚህ እናስተውላለን፤ ለጠላቶቹ ሕይወት ፍቅርና ሰላም ሲል እነሱን ከመሆን አልፎ እስከ ቤዛዊ መሥዋዕት የሚዘልቅ ፍቅር እጅግ በጣም ታላቅ ነው፤ የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት ! እግዚአብሔር ለእኛ ያለው ፈቃድ እኛ በሕይወት በሰላምና በፍቅር እንድንኖርለት ከሆነ የእኛ ግብረ መልስም ከዚህ የተለየ ሊሆን ኣይገባም፤ እግዚአብሔር ጠላቶቹን ለማዳን እንጂ ለማጥፋት አልመጣም፤ የእኛም ሕይወት የሚጠበቀው ኣንዱ ሌላውን በማዳን እንጂ በማጥፋት እንዳልሆነ ጌታችን በቃልም በተግባርም በኣጽንዖት ነግሮናል፤ በዚህ አስተሳሰብና እምነት እንድንኖርም አዞናል፡፡ታድያ በቃሉ ለመኖርና ለእሱ ለመታዘዝ ቃል የገባን እኛ ክርስቲያኖች ይህን ሁሉ እርግፍ ኣድርገን በመተው እርስ በእርስ ለመጠፋፋት መሽቀዳደም ምን ይሉታል? ይህስ ለማን ይበጃል?የአንድ ሀገር ሕዝቦች ይመካከራሉ፣ ይቻቻላሉ፣ ይታገሣሉ፣ ጊዜ ሰጥተው ያስቡና መፍትሔ ያበጃሉ እንጂ ማን በማን ላይ ይነሣል? ይህ ለማንኛችንም አይበጀንምና ወደ ኣእምሮኣችን እንመለስ የሚል ጥሪ የወቅቱ የቤተ ክርስቲያናችን መልእክት ነው፤ በመጨረሻም፤ ይህንን የተቀደሰ በዓል ስለ ሃገራችን ዘላቂ ሰላም በመጸለይና በማሰብ እንዲሁም በልዩ ልዩ  ምክንያት የምግብ፣ የልብስና የመጠለያ እጥረት ያጋጠማቸው ወገኖቻችንን በመደገፍና በመርዳት ለእግዚአብሔር ክብር ብለን ለሀገር ኣንድነትና ለሕዝብ ፍጹም ሰላም መስፈን ከልብ በመነሣሣት በዓሉን እንድናከብር አባታዊ ጥሪያችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን!! መልካም በዓለ ልደት ያድርግልን!!እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ ወስብሐት ለእግዚአብሔር  አሜን!አባ ማትያስ ቀዳማዊፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ታኅሣሥ ፳፱ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ምአዲስ አበባ ኢትዮጵያ ©EOTC TV

ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ልደቱ ለእግዚእነ ወአምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ  ዘዕሥራ ምእት ዓሠርቱ ወሰምንቱ ዓመት ምሕረት Read More »

በሀገረ ስብከቱ ያሉ ተግዳሮቶችን ለመፍታት የሚያስችል የምክክር መድረክ ተካሄደ!

ኤክቱስ ታኅሣሥ 27/2018 ዓ.ም በጌዴኦ ኮሬና ቡርጅ ሀገረ ስብከት የሚታዩ ዘርፈ ብዙ የአገልግሎትና የአስተዳደር ተግዳሮቶችን በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችል የሀሳብና የገንዘብ ድጋፍ የማሰባሰቢያ መርሃ ግብር በአዲስ አበባ ሸራተን ሆቴል ተካሂዷል። መርሃግብሩ በብፁዕ አቡነ ገሪማ የሀገረ ስብከቱ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል መሪነት በተቋቋመው መማክርት ጉባኤ አባላት የተዘጋጀ ነው። በዚሁ የምክክር መድረክ ላይ ብፁዕነታቸውን ጨምሮ ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የደቡብ ኦሞና የአሪ ዞኖች ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት የቅዱስ ሲኖዶስ አባል፣ መልአከ ብርሃን አጥናፉ ማሞ የሀገረ ስብከቱ ዋና ጸሐፊ እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው የተለያዩ ተጽዕኖ ፈጣሪ አካላት ተገኝተዋል። ​ብፁዕ አቡነ ገሪማ የሀገረ ስብከቱን የቀድሞና ወቅታዊ ሁኔታ የሚዳስስ ሰፊ የሁኔታዎች መግለጫ (Presentation) አቅርበዋል። በመግለጫውም በሀገረ ስብከቱ ሥር በሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት የሚታዩ ዋና ዋና ችግሮች የተዳሰሱ ሲሆን፣ በተለይም በገጠር አካባቢዎች የሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት በከፊልና ሙሉ ለሙሉ ተዘግተው መቆየታቸው ትልቅ ትኩረት የሚሻ ጉዳይ መሆኑ ተመላክቷል። እነዚህን የተዘጉ አብያተ ክርስቲያናት በአፋጣኝ አገልግሎት እንዲጀምሩ ማድረግ በቀጣይ ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር መሆኑም ገልጸዋል።​ከአብነት ትምህርት መስፋፋት ጋር ተያይዞ በሀገረ ስብከቱ ያለውን ክፍተት ለመሙላት በአሁኑ ወቅት በአንዲዳ የአዳሪ የአብነት ትምህርት ቤት መጀመሩን ገልጸዋል። ሆኖም ግን ይህ ጅምር ካለው ስፋት አንጻር በቂ ባለመሆኑ፣ የአብነት ትምህርት ቤቶችን በስፋት ማደራጀትና በቋንቋ የሚያገለግሉ ካህናትና ዲያቆናትን ማፍራት እንደሚገባ በሰፊው አንስተዋል። ​በስብከተ ወንጌል ረገድም በአብዛኞቹ አድባራት ሰባክያነ ወንጌል ባለመኖራቸው ምክንያት ምዕመናን ተገቢውን መንፈሳዊ ትምህርት በማግኘት ላይ እንዳልሆኑ ተጠቅሷል። ይህን የስብከተ ወንጌል እጥረት ለመቅረፍና ወንጌልን ለሁሉም ተደራሽ ለማድረግ በአከባቢው ቋንቋ የሚያገለግሉ ሰባክያንን በማሰልጠንና በመመደብ ረገድ ሰፊ ሥራ እየተሠራ መሆኑና ይህ በቂ አለመሆኑን በመድረኩ ላይ አንስተዋል። ​የሀገረ ስብከቱን የአስተዳደር ስራዎች ከዘመኑ ጋር ለማስማማትና የአሰራር ድክመቶችን ለማስተካከል ታሳቢ ያደረጉ የለውጥ ሀሳቦችም አቅርበዋል። የሀገረ ስብከቱ መዋቅር ይበልጥ እንዲጠናከርና ለምዕመናን የሚሰጠው አገልግሎት እንዲሳለጥ አስተዳደራዊ ማሻሻያዎችን ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ለውይይቱ ተሳታፊዎች አስገንዝበዋል። ​በመጨረሻም የመርሃ ግብሩ ተሳታፊዎች በቀረቡት ዝርዝር ችግሮችና የመፍትሄ አቅጣጫዎች ላይ ከተወያዩ በኋላ ሀገረ ስብከቱን በሁሉም ረገድ ለመደገፍ ቃል ገብተዋል። ይህም ድጋፍ በእውቀት፣ በገንዘብና በጉልበት እንደሚሆን በመግለጽ ሀገረ ስብከቱ የተደቀኑበትን ችግሮች ተሻግሮ ተልዕኮውን እንዲወጣ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ለማድረግ ቃል ገብተዋል።

በሀገረ ስብከቱ ያሉ ተግዳሮቶችን ለመፍታት የሚያስችል የምክክር መድረክ ተካሄደ! Read More »

ማስታወቂያ

የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጽሕፈት ቤት ለዲላ ደብረ ሰላም ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ በቋሚ ጸሐፊ መደብ ሠራተኛ ለመቅጠር ባወጣው ማስታወቂያ የወጣውን መስፈርት ያሟላችሁ ብቻ የሥራ ልምድና የድጋፍ ደብዳቤ በመያዝ ማግሰኞ ጥር 5/2018 ዓ.ም ከረፋዱ 4:00 ሰዓት በሀገረ ስብከቱ ጽሕፈት ቤት ለፈተና እንድትገኙ እየገለጽን በማስታወቂያው የተገለጸውን መሥፈርት የማያሟላ ተመዝጋቢ ለፈተና የማይቀመጥ መሆኑን ከወዲሁ እናሳውቃለን። ኤክቱስ ታኅሣሥ 23/2018 ዓ.ም

ማስታወቂያ Read More »

፲፩ኛው ዙር የወጣቶች መርሃግብር በዲላ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ስለተዘጋጀ ሁላችሁም እንድትገኙ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን!

ኤክቱስ ታኅሣሥ 21/2018 ዓ.ም

፲፩ኛው ዙር የወጣቶች መርሃግብር በዲላ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ስለተዘጋጀ ሁላችሁም እንድትገኙ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን! Read More »

አስራ ስምንት አዳዲስ አማንያን የሥላሴን ልጅነት አገኙ!

ኤክቱስ ታኅሣሥ 19/2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት በኮሬ ወረዳ ቤተ ክህነት በቆሬ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን የታላቁ መልአክ የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ የንግሥ በዓል በደመቀ ሁኔታ ተከብሯል። በበዓሉ አስራ ስምንት አዳዲስ አማንያን በጥምቀት የሥላሴን ልጅነት አግኝተዋል። መረጃውን ያደረሱን የወረዳ ቤተ ክህነቱ ዋና ጸሐፊ ናቸው።

አስራ ስምንት አዳዲስ አማንያን የሥላሴን ልጅነት አገኙ! Read More »

የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል በጪጩ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ብፁዕ አቡነ ገሪማ በተገኙበት በታላቅ መንፈሳዊ ድምቀት ተከበረ!

ኤክቱስ ታኅሣሥ 19/2018 ዓ.ም ሁልጊዜም ታኅሣሥ አስራ ዘጠኝ ቀን የሚከበረው የታላቁ መልአክ የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በጪጩ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲይና የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ብፁዕ አቡነ ገሪማ በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተከብሯል። ታቦቱ ከመንበሩ ከመውጣቱ በፊት መምህር እስራኤል ብርሃኑ በጌዴኡፋ ቋንቋ ለዕለቱ የሚሆን ትምህርት አስተምረዋል። ታቦቱ ከመንበሩ ከወጣ በኋላ በደብሩ የሰንበት ትምህርት ቤት ዘማርያን ወረብ ቀርቦ የዲላ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ሥራ አስኪያጅ አቶ ማዘንጊያ ኢያቶ ንግግር አድርገዋል። በመቀጠል በመጋቤ ሐዲስ ዮሐንስ ማሞ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የስብከተ ወንጌል ሐዋርያዊ አገልግሎት መምሪያ ሰባኬ ወንጌልና የታላቁ የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ አስተዳደር ምክትል ዲን የዕለቱ ትምህርት ተሰጥቷል። ስእለት፣ መባ እና ሥጦታ የመቀበል መርሃግብር በመምህር ስንታየሁ እና በሊቀ ትጉሃን ሀብታሙ አበበ ተከናውኗል። በመጨረሻም በሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ በመልአከ ሕይወት ብርሃኑ ክፍሌ ጋባዥነት ብፁዕነታቸው ለሕዝቡ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ በመስጠት በጸሎት ፈጽምዋል።

የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል በጪጩ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ብፁዕ አቡነ ገሪማ በተገኙበት በታላቅ መንፈሳዊ ድምቀት ተከበረ! Read More »

ብፁዕ አቡነ ገሪማ ጳጳስ ለአርባ ደቀ መዛሙርት ሥልጣነ ክህነት ሰጡ!

ኤክቱስ ታኅሣሥ 19/2018 ዓ.ም ብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል የታኅሣሥ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል በሚከበርበት በጪጩ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ተገኝተው ለ33 ደቀ መዛሙርት የዲቁና ለ7 ዲያቆናት የቅስና በአጠቃላይ ለ40 ደቀመዛሙርት ሥልጣነ ክህነት ሰጥተዋል። ደቀ መዛሙርቱ ለዲቁና እና ለቅስና የሚያበቃቸውን መንፈሳዊ ትምህርት ሲከታተሉ የቆዩ ሲሆኑ ከመሾማቸው በፊትም ብቁ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ፈተና ተሰጥቷቸው ማለፋቸው ተገልጿል። ብፁዕነታቸው በሰጡት አባታዊ ቃለ ምዕዳን ክህነት ትልቅ ኃላፊነት መሆኑን አሳስበው አዲሶቹ አገልጋዮች መንጋውን በንጽሕና፣ በትጋትና በቅንነት እንዲጠብቁ አደራ ብለዋል።

ብፁዕ አቡነ ገሪማ ጳጳስ ለአርባ ደቀ መዛሙርት ሥልጣነ ክህነት ሰጡ! Read More »

Scroll to Top