በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት

Public Relation

የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ለዲላ ዋለሜ ሰዓሊተ ምሕረት ኪዳነ ምሕረት፣ ለወናጎ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም እና ለጨለለቅቱ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም አብያተ ክርስቲያናት የመጽሐፍ መምህራንን ለመቅጠር ባወጣው ማስታወቂያ መሠረት መስፈርቱን አሟልተው የተገኙ እጩ(ዎች) ያመጡት አጠቃላይ የፈተና ውጤት!

ኤክቱስ ሐምሌ 6/2018 ዓ.ም

የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ለዲላ ዋለሜ ሰዓሊተ ምሕረት ኪዳነ ምሕረት፣ ለወናጎ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም እና ለጨለለቅቱ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም አብያተ ክርስቲያናት የመጽሐፍ መምህራንን ለመቅጠር ባወጣው ማስታወቂያ መሠረት መስፈርቱን አሟልተው የተገኙ እጩ(ዎች) ያመጡት አጠቃላይ የፈተና ውጤት! Read More »

ብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል በተገኙበት ዓመታዊውን የቅድስት ሥላሴን የንግሥ በዓል ምክንያት በማድረግ በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት በዲላና ወናጎ ወረዳ ቤተ ክህነት በዲላ መካነ ቅድስት ሥላሴ ወአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን የተዘጋጀው የሁለተኛ ቀን መንፈሳዊ ጉባኤ!

ኤክቱስ ሐምሌ 5/2018 ዓ.ም

ብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል በተገኙበት ዓመታዊውን የቅድስት ሥላሴን የንግሥ በዓል ምክንያት በማድረግ በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት በዲላና ወናጎ ወረዳ ቤተ ክህነት በዲላ መካነ ቅድስት ሥላሴ ወአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን የተዘጋጀው የሁለተኛ ቀን መንፈሳዊ ጉባኤ! Read More »

“ምሥጢራተ ማኅሌት ዘመላእክት” የተሰኘው አዲስ መጽሐፍ ብፁዕነታቸው በተገኙበት ተመረቆ ለንባብ በቃ!

ኤክቱስ ሐምሌ 5/2018 ዓ.ም በጌዴኦ ኮሬና እና ቡርጂ ሀገረ ስብከት የአንዲዳ የአዳሪ የአብነት ትምህርት ቤት ኃላፊ በመጋቤ ምሥጢር ጥበቡ አናጋው የተዘጋጀው “ምሥጢራተ ማኅሌት ዘመላእክት (ቁጥር ሁለት)” የተሰኘው አዲስ መጽሐፍ ሐምሌ 5 ቀን 2018 ዓ.ም. በታላቅ ድምቀት ተመርቆ ለንባብ በቅቷል። የመጽሐፍ ምርቃቱ መርሃ ግብር ብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ ኮሬና እና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል መሪነት በጸሎተ ወንጌል ተከፍቶ የተጀመረ ሲሆን በመቀጠልም የዕለቱን ትምህርት መምህር መልአክ መሰለ በሰፊው አስተምረዋል። በተጨማሪም በመርሃ ግብሩ ላይ በዘማርያን ዝማሬ እንዲሁም በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ቅኔ ቀርቧል። በዚሁ የምርቃ ሥነ ሥርዓት ላይ የሀገረ ስብከቱ የፕሮጀክት ማናጀር ቀሲስ ጤናው እንዳላማው ሰፊ የመጽሐፍ ዳሰሳ አቅርበዋል። ቀሲስ ጤናው በዳሰሳቸው ላይ እንደገለጹት ይህ መጽሐፍ በ፮ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በኢትዮጵያዊው ሊቅ በቅዱስ ያሬድ የተደረሱትንና በሰማያውያን መላእክት ሥርዓተ አምልኮ ላይ የተመሰረቱትን ረቂቅ ምሥጢራት፣ የዜማ ስልቶችንና የቅዱሳን መላእክትን የምሥጋና ምሥጢር ከቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ጋር በማገናኘት በሰፊው የሚተነትን የምርምር ሥራ ነው። አዘጋጁ መጋቤ ምሥጢር ጥበቡ አናጋው ለመጽሐፉ ዝግጅት ቅዱሳት መጻሕፍትን፣ አምስቱን የያሬዳዊ ዜማ መጻሕፍትን፣ የሊቃውንት የአንድምታ ትርጓሜዎችን እንዲሁም ጥንታውያን ድርሳናትንና ገድላትን በዋቢነት መጠቀማቸው የመጽሐፉን ምሁራዊና ሥርዓታዊ ጥንካሬ ከፍ እንዳደረገው በዳሰሳው ተብራርቷል። መጽሐፉ ለመደበኛው አንባቢያን አስቸጋሪ ሊሆኑ የሚችሉትን የግዕዝ ቃላትና የዜማ ምልክቶች ወደ አማርኛ በሚገባ በመተርጎም፣ ምስጢሩ በቀላልና ማራኪ ስልት እንዲቀመጥ ማድረጉም ተገልጧል። በመርሃ ግብሩ ማጠቃለያ ላይ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ገሪማ አባታዊ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ የሰጡ ሲሆን በእምነትና በዕውቀት ለማደግ ንባብ ወሳኝ በመሆኑ ሁሉም ምዕመን አንባቢ መሆን እንዳለበት አሳስበው ሰፊ መልዕክት አስተላልፈዋል። የምርቃቱ ሥነ ሥርዓትም በብፁዕነታቸው ጸሎትና ቡራኬ ተጠናቋል።

“ምሥጢራተ ማኅሌት ዘመላእክት” የተሰኘው አዲስ መጽሐፍ ብፁዕነታቸው በተገኙበት ተመረቆ ለንባብ በቃ! Read More »

ለገጠር አብያተ ክርስቲያናት የንዋየ ቅድሳት ድጋፍ ተደረገ!

ኤክቱስ ሐምሌ 5/2018 ዓ.ም በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ሥር ለሚገኙ በንዋየ ቅድሳት እጥረት ምክንያት የተሟላ መንፈሳዊ አገልግሎት ለማይሰጥባቸው የገጠር አብያተ ክርስቲያናት ፤ አረጋዊው ርእሰ ደብር ቀሲስ ለገሰ በለጠ ወልደ ሚካኤል፣ ወልደ ገብርኤል፣ ፍቅረ አማኑኤል፣ ኃይለ ማርያም፣ ኃይለ ገብርኤል እና ወልደ አረጋዊ የተባሉ መንፈሳዊ ልጆቻቸውን በማስተባበር የሁለት ሰሞነኛ ሙሉ ልብሰ ተክኅኖ፣ ሀዲስ ኪዳን፣ ተአምረ ማርያም፣ መዝገበ ቅዳሴ ከነምልክቱ (በጉልህ) እና መጽሐፈ ግጻዌ ራሳቸው አስደጉሰው ድጋፍ አድርገዋል። ድጋፉን ብፁዕ አቡነ ገሪማ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል የተረከቡ ሲሆን ድጋፍ ላደረጉት አካላት ምስጋና አቅርበው ሌሎችም ምዕመናን በዚህ ተግባር እንዲሳተፉ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

ለገጠር አብያተ ክርስቲያናት የንዋየ ቅድሳት ድጋፍ ተደረገ! Read More »

መልአከ ፀሐይ ቀሲስ ሙላት ግዛው የዲላ ዳግማዊት ጌቴሴማኒ በአታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ ተደርገው ተመደቡ!

ኤክቱስ ሐምሌ 5/2018 ዓ.ም በብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል መልካም ፈቃድ መልአከ ፀሐይ ቀሲስ ሙላት ግዛው በዲላና ወናጎ ወረዳ ቤተ ክህነት የዲላ ዳግማዊት ጌቴሴማኒ በአታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ ተደርገው ተመድበዋል። በዕለቱ የትውውቅ መርሃግብር የተደረገ ሲሆን መልአከ ሰላም ቆሞስ አባ ዮሐንስ ምሕረቱ ደብዳቤውን ያነበቡ ሲሆን ስብከተ ወንጌልን በማስፋፋት፣ ሰንበት ትምህርት ቤትን በማጠናከር፣ የልማት ሥራዎችን በማስፋፋት፣ ማኅበረ ካህናትንና ምዕመናንን በፍቅር በአንድነት መምራት እንደሚገባ እንዲሁም ምዕመናን ከአዲሱ አስተዳዳሪ ጋር በመሆን በአንድነት ሊሠሩ እንደሚገባ ገልጸዋል። የዕለቱን ትምህርት አዲሱ የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ፀሐይ ቀሲስ ሙላት ግዛው አስተምረው ትውውቅ አድርገዋል። በዕለቱ የወረዳ ቤተ ክህነቱ ዋና ጸሐፊ ሊቀ ኅሩያን እሸቱ ዋለ፣ የደብሩ ካህናትና መምህራን፣ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ አስተዳደር አካላት እንዲሁም ምዕመናን ተገኝተዋል።

መልአከ ፀሐይ ቀሲስ ሙላት ግዛው የዲላ ዳግማዊት ጌቴሴማኒ በአታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ ተደርገው ተመደቡ! Read More »

የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጽሕፈት ቤት በመጽሐፍ መምህር መደብ ሠራተኛ ለመቅጠር ባወጣው ማስታወቂያ መሠረት የተመዘገባችሁ ሰኞ ሐምሌ 06/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት በሀገረ ስብከቱ ጽሕፈት ቤይ ለፈተና እንድትቀርቡ ስንል እናስታውቃለን!

ኤክቱስ ሰኔ 29/2018 ዓ.ም

የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጽሕፈት ቤት በመጽሐፍ መምህር መደብ ሠራተኛ ለመቅጠር ባወጣው ማስታወቂያ መሠረት የተመዘገባችሁ ሰኞ ሐምሌ 06/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት በሀገረ ስብከቱ ጽሕፈት ቤይ ለፈተና እንድትቀርቡ ስንል እናስታውቃለን! Read More »

ብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ለሁለተኛ ዙር የአንዲዳ የአዳሪ የአብነት ትምህርት ቤት ምረቃ መርሃ ግብር ላይ ያስተላለፉት መልእክት!

ኤክቱስ ሰኔ 27/2018 ዓ.ም “ቡሩክ ዘይመጽእ በስመ እግዚአብሔር ባርክናክሙ እምቤተ እግዚአብሔር – በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ ቡሩክ ነው በእግዚአብሔር ስም መረቅናችሁ” መዝ 117፥26 ውድ የቤተ ክርስቲያን ልጆች በመጀመርያ በዚህ ታላቅና ታሪካዊ የሁለተኛ ዙር የምረቃ መርሃግብር ላይ አብራችሁን ስላላችሁ በቅድሚያ “እንኳን ደኅና መጣችሁ” ለማለት እንወዳለን። ዛሬ የምንገኘው ለአሥር ወራት የተሰጣቸውን ትምህርት ሌሊት ከቀን በከፍተኛ ትጋት ሲከታተሉ የቆዩትን ደቀ መዛሙርቶቻችንን የምርቃት በዓል ለማክበር ነው። ውድ ደቀ መዛሙርት ሆይ ለዚህ ታላቅ ማዕረግና ስኬት በመብቃታችሁ “እንኳን ደስ አላችሁ” እያልኩ “ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው” የሚለውን አምላካዊ ተልዕኮ ተቀብላችሁ በጥንካሬና በብቃት እንድትወጡ መልካም ምኞታችንን እንገልጻለን። ወድ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን በሀገረ ስብከታችን ከ2016 ዓ.ም በፊት ምንም ዓይነት የተደራጀ የአብነት ትምህርት ቤት ባለመኖሩ በገጠሪቱ ቤተ ክርስቲያን ውዳሴ ማርያም በአግባቡ የተማረ ዲያቆን ማግኘት የማይቻልበት ደረጃ ላይ ደርሶ ነበር። በዚህ ረገድ ያለውን ችግር ከመቅረፍ አንጻር ሀገረ ስብከታችን የ10 ዓመት ሥልታዊ ዕቅድን ከምንም ተነስቶ በቁርጠኝነት አሳካዋለሁ ብሎ ያስቀመጠውን ግብ ወደ ተግባራዊ ዕቅድ በመቀየር አንድ ብሎ በ2017 ዓ.ም ጉዞውን በስድስት ደቀ መዛሙርት መቃብር ቤቶችን በማደስ፣ ቀለባቸውን፣ መኝታቸውንና ሕክምናቸውን ጨምሮ ሙሉ ወጫቸውን በመሸፈን ጀመረ። ይህ በቅንነት የተዘራአ ዘር አድጎና ጎምርቶ በ2018 ዓ.ም አቅሙን በማሳደግ 17 ደቀ መዛሙርትን ተቀብሎ ማስተማር ችሏል። ዛሬ የምናስመርቃቸው ከእነዚህ ውስት 14ቱን ሲሆን ሦስቱ የሐዲሳት ደቀ መዛሙርት በመሆናቸው ለቀጣዩ ሦስት ዓመታት ከትምህርት ቤቱ ጋር የሚዘልቁ ናቸው። የዚህ የአብነት ትምህርት ቤት ጉዞ በአጭር ጊዜ ውስጥ ያሳየው ዕድገት የእግዚአብሔር ቸርነት ታክሎበት የእናንተ ልግስና ውጤት በመሆኑ እንኳን ደስ አላችሁ። ይህ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲሳካ በተለይም የደቀ መዛሙርቱን የቀለብና የዕለተዕለት ፍላጎት በመደፍ መንፈሳዊ ግዴታችሁን የተወጣችሁ ማኅበረ ቅዱሳን ዋና ማእከል፣ ማኅበረ አቡቀለምሲስ እና ሊቀ ሊቃውንት ስምዐ ኮነ መልአክ ከኢትዮጵያ… መልአከ ሣህል ቀሲስ አወቀ፣ ቤተልሔምና ቤተሰቦቿ፣ እኅታችን ሃና ከአሜሪካ እንዲሁም የሀገረ ስብከታችን መማክርት ጉባኤ የእናንተ እጅ መዘርጋት ዛሬ ስለምናየው ፍሬ መሠረት ሆኗልና በእግዚአብሔር ስም የላቀና የከበረ ምሥጋናዬን በሀገረ ስብከታችን ስም አቀርባለሁ። በመቀጠልም ጉዟችን በዚህ ብቻ የሚያበቃ ባለመሆኑ ለ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የትምህርት ቤቱን አቅም ይበልጥ በማሳደግ በማኅበረ ቅዱሳን ዋና ማዕከል ለ32 ደቀ መዛሙርት የሚሆን ዶርሚተሪ፣ መመገቢያ አዳራሽና ማብሰያ፣ የሁለት መምህራን መኖርያ ቤት፣ እንዲሁም ለሁሉም የሚያገለግል የሻወርና የሽንት ቤት ግንባታ ተጀምሮ ሥራው በመፋጠን ላይ ይገኛል። በመሆኑም በቀጣይ የትምህርይ ዘመን አዳዲስ ተማሪዎችን ለመቀበል በከፍተኛ ዝግጅት ላይ እንገኛለን። ይህ ትልቅ ራዕይና የጀመርነው የልማት ሥራ ዳር እንዲደርስ እንዲሁም ወደፊት ብዙ ደቀመዛሙርትን አፍርተን ለቤተ ክርስቲያን ለሀገር እንድናበረክት ውድ የቤተ ክርስቲያን ልጆች ደጋፊዎቻችን ከጎናችን እንዳትለዩ የወደፊት እርዳታችሁንና ድጋፋችሁን አጠናክራችሁ እንድትቀጥሉ እያሳሰብኩ ለአንድ ደቀ መዝሙር አንድ ሰው በሚል መሪ ቃል ምእመናንን የዚህ በረከት ተሳታፊዎች እንዲሆኑ ለማድረግ የጀመርነውን ተግባር ለሌሎች እንዲዳረስ ታደርጉ ዘንድ በታላቅ ትህትና እናሳስባለን። በመጨረሻም የሁለተኛ ዙር የአብነት ትምህርት ቤት የምረቃ መርሃግብር በይፋ መጀመሩን እያበሰርን መልካም የደስታና የበረከት ጊዜ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ። እግዚአብሔር ሀገራችንን ይባርክ!                       አባ ገሪማየጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስናየቅዱስ ሲኖዶስ አባል

ብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ለሁለተኛ ዙር የአንዲዳ የአዳሪ የአብነት ትምህርት ቤት ምረቃ መርሃ ግብር ላይ ያስተላለፉት መልእክት! Read More »

ብፁዕነታቸው በተገኙበት የሀገረ ስብከቱ የመማክርት ጉባኤ ከዲላው መንበረ ጵጵስና ሕንጻ አሠሪ ኮሚቴ ጋር ውይይት አካሄደ!!

ኤክቱስ ሰኔ 26/2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ የሚገኘው የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት የመማክርት ጉባኤ አባላት በዛሬው ዕለት ወደ ዲላ ከተማ በመምጣት ጉብኝት አድርገዋል። በጉብኝቱም ወቅት በግንባታ ላይ የሚገኘው የመንበረ ጵጵስና ሕንጻ አሁናዊ ሁኔታና የደረሰበት ደረጃ በአካል ተመልክቷል። የመማክርት ጉባኤው ከተጠናቀቀው የመስክ ምልከታ በኋላ ከመንበረ ጵጵስና ሕንጻ አሠሪ ኮሚቴ አባላት ጋር ውይይት አድርጓል። በውይይቱም ወቅት የሕንጻ ግንባታው ያለበት አጠቃላይ ደረጃና በቀጣይ መከናወን በሚገባቸው አንገብጋቢ የሥራ ሂደቶች ላይ በስፋት መክረዋል። በዚህ የጋራ የውይይት መድረክ ላይ ብፁዕ አቡነ ገሪማ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ተገኝተዋል። ብፁዕነታቸው ለጉባኤውና ለኮሚቴው አስፈላጊውን አባታዊ መመሪያና ምክር የሰጡ ሲሆን የሥራ እንቅስቃሴው በተቀናጀ መልኩ እንዲቀጥል አሳስበዋል። የመማክርት ጉባኤውና የመንበረ ጵጵስና ሕንጻ አሠሪ ኮሚቴዎች በጋራ ባደረጉት ምክክርም ግንባታውን በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ የሚያስችል የጋራ የሥራ ስምምነት ላይ በመድረስ ውይይታቸውን አጠናቀዋል።

ብፁዕነታቸው በተገኙበት የሀገረ ስብከቱ የመማክርት ጉባኤ ከዲላው መንበረ ጵጵስና ሕንጻ አሠሪ ኮሚቴ ጋር ውይይት አካሄደ!! Read More »

፲፮ኛው ዙር የወጣቶች መርሃግብር በዲላ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ሰኔ 28/2018 ዓ.ም ስለተዘጋጀ ሁላችሁም ከቀኑ 7:00 ጀምሮ ተገኝታችሁ የመርሃግብሩ ተሳታፊዎች እንድትሆኑ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን!

ኤክቱስ ሰኔ 26/2018 ዓ.ም

፲፮ኛው ዙር የወጣቶች መርሃግብር በዲላ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ሰኔ 28/2018 ዓ.ም ስለተዘጋጀ ሁላችሁም ከቀኑ 7:00 ጀምሮ ተገኝታችሁ የመርሃግብሩ ተሳታፊዎች እንድትሆኑ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን! Read More »

ለሦስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው መንፈሳዊ ጉባኤ በብፁዕነታቸው ቡራኬ ተጠናቀቀ!

ኤክቱስ ሰኔ 22/2018 ዓ.ም በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት በኮቾሬ ገደብና ጮርሶ ወረዳዎች ቤተ ክህነት በጨለለቅቱ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ለሦስት ተከታታይ ቀናት ሲካሄድ የቆየው ዐቢይ መንፈሳዊ ጉባኤ ተጠናቋል። የጉባኤው ዋና ዓላማ ከቤተ ክርስቲያን የራቁ ምዕመናንን ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንዲመጡ ለማድረግ ሲሆን በተጨማሪም የቅዱሳን ምሥጢራትን ሡታፌ ለማሳደግ ያለመ ነው። በጉባኤው የተገኙት መምህራን ሊቀ ሊቃውንት ዮሴፍ ደሳለኝ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሊቃውንት ጉባኤ አባል፣ መጋቤ ሀዲስ አድነው ወንድሙ በተለያዩ ርእሰ ጉዳዮች ዙርያ ሰፊ ትምህርት ሲሰጡ ቆይተዋል። በተጨማሪም በዝማሬ ሙዐዘ ስብሐት ዳግማዊ ደርቤ፣ ዘማሪት ምርትነሽ ጥላሁንና ዘማሪ ጌታሁን ታደሰ (በጌዴኡፋ ቋንቋ) ሲያገለግሉ ቆይተዋል። በመጨረሻም ብፁዕነታቸው በጉባኤው እጅግ መደሰታቸውን የገለጹ ሲሆን ከሩቅ ሀገር ለስብከተ ወንጌል አገልግሎት የመጡት መምህራንና ዘማርያንን፣ ይህንን ጉባኤ ያዘጋጁትን የደብሩ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ አስተዳደርን በአጠቃላይ ተሳትፎ ያላቸውን አካላት በሙሉ አመስግነዋል።በተጨማሪም በጌዴኡፋ ቋንቋ ዝማሬ ያቀረቡ ሲሆን አባታዊ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ሰጥተው በጸሎት ፈጽመዋል።

ለሦስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው መንፈሳዊ ጉባኤ በብፁዕነታቸው ቡራኬ ተጠናቀቀ! Read More »

Scroll to Top