“የአትትዎ ለኀጥእ ከመኢይርአይ ስብሐተ እግዚአብሔር – የእግዚአብሔርን ክብር እንዳያይ ኀጢአተኛውን ሰው ያርቁታል”ኢሳ ፳፮፥፲
ቃሉን የተናገረው ነቢየ ልዑል ኢሳይያስ ሲሆን ለጊዜው ለሰናክሬምና ለአሥሩ ነገድ የተነገረ ነው።ፍጻሜው ግን ለይሁዳ የተነገረ ነው። ይሁዳ በስም ተስፋ በግብር ዘለፋ የሆነ ያልታደለ ፍጡር ነው (ማቴ26፥24) የእግዚአብሔርን ክብር ለማየት ፣እምነትና ቅድስና ያስፈልጋል። ያለ እምነትና ያለቅድስና የእግዚአብሔር የክብሩ ተካፋይ መሆን አይቻልም። (ዕብ11፥6) እግዚአብሔር ጻድቀ ባሕር፣ ንጹሐ ባሕርይ ነውና ያላመነ ልቡና ፣ ንስሓ ያልገባ ሰብእና ያለውን ሰው ኀጢአት ግድግዳም ሆኖ ፣ ገደልም ሆኖ ከእግዚአብሔር ያርቀዋል (ሉቃ16፥26) የእግዚአብሔርን ክብር አያያም። በዛሬው በዓል አዕማድ ተብለው የሚጠሩት (ገላ3፥9) የእምነት ፣የፍቅርና የወንጌል ሰዎች ቅዱስ ጴጥሮስ ጴጥሮስ፣ ቅዱስ ዮሐንስና ቅዱስ ያዕቆብ የእግዚአብሔርን ክብር ያዩበት፣ የእምነት የፍቅር፣ የንስሓ ሰው ያልሆነው የአስቆሮቱ ይሁዳ ደግሞ የእግዚአብሔርን ክብር እንዳያይ ኀጢአት ከእግዚአብሔር የማያገናኝ ገደል ሆኖ አርቆታል። የእግዚአብሔር ክብር ወደሚገለፅበት ተራራ መውጣት አልቻለም። ይሁዳ ብቻ ሳይሆን 8ቱ ደቀ መዛሙርትም ክብሩን ቢያዩም ወደተራራው እንዳይወጡ የሆኑበት ምክንያት የይሁዳ ኀጢአት ነው። የእኛ ኀጢአት ከእኛ ባለፈ ለሌላውም ይተርፋል። “ለኀጥአን የወረደ ለጻድቃን ይተርፋል” አይደል የሚባለው? በዓሉ ከጌታ 9 ዐበይት በዓላት አንዱ ነው የበዓሉ ስያሜም ደብረታቦር ይባላል ደብረ ታቦር ማለትም ታቦር የሚባል ተራራ ማለት ነው። ማቴዎስ ፣ማርቆስና ሉቃስ ረዥም ተራራ ከማለት በቀር ታቦር ብለው አልገለፁም ዮሐንስ ጨርሶ ከነታሪኩ አያነሣም ቅዱስ ጴጥሮስም “በቅዱሱ ተራራ ሳለን”2ኛ ጴጥ1፥18 አለ እንጂ ታቦር ብሎ አልነገረንም የሐዋርያት ሲኖዶስና የቤተክርስቲያን ትውፊት ታቦር እንደሆነ ያስረዳሉ። ነቢዩ ዳዊትም “ታቦር ወአርሞንኤም ይትፌሥሑ በስመ ዚኣከ”ብሎ አንሥቶታል። በዚህ በዓል የምናከብረው ታራራውን አይደለም ።ጴጥሮስ ቅዱሱ ተራራ ብሎ እንደጠራው የእግዚአብሔር ክብር የተገለጠበት የአብ ድምፅ የተሰማበት የብሉይኪዳንና የሐዲስ ኪዳን ቅዱሳን የተገናኙበት የቤተ ክርስቲያን ምሳሌ የሆነ ቅዱስ ሥፍራ ቢሆንም በዓሉ የተራራው አይደለም።በዓላትን ቤተክርስቲያን በሦስት መንገድ ስያሜ ትሠጣለች አንደኛ ቀጥታ ስምን በመውሰድ ነው በስም ሚካኤል፣ ገብርኤል ፣ አማኑኤል ሁለተኛ በድርጊት ፅንሰት፣ልደት፣ስቅለት ሦስተኛ በቦታ ቁስቋም፣ደብረ ዘይት ፣ደብረ ታቦር ይባላል ከቅኔ ቤት ትውስታዬ የደብረ ታቦር በዓል ጊዜ አንድ ተማሪ ለአንድ መነኩሴ የተቆረሰ ዳቦ አንሥቶ ስለደብረ ታቦር አላቸው እሳቸውም ተራራው ይሥጥልኝ ብለው ተቀበሉ የምንዘክረው ታራራውን ሳይሆን ክርስቶስን ነው ማለታቸው ነበር።ይህ ተራራ ከገሊላ ተራራ በምዕራብ በኩል 10 ኪሎ ሜትር የራቀ ሲሆን ከባሕር ወለል በላይ 572 ሜትር ከፍታ ያለው፣ የተራራው አናት 1000 ሜትርበ400 ሜትር ስፋትያለው ደልዳላ መስክ ያለበት ተራራ እንደሆነ ባለሙያዎች ይገናገራሉ። ነገደ ዛብሎን፣ነገደ ንፍታሌምና ነገደይሳኮር የሚገናኙበትነው።ታሪኩ በማቴ 17፥1-9 በማር9፥1በሉቃ 9፥28 እንደተመዘገበው ኢየሱስ ጴጥሮስን፣ያዕቆብንና ዮሐንስን ይዞ ወደረዥም ተራራ ወጣ በፊታቸውም ተለወጠ ፊቱም እንደፀሐይ በራ ልብሱም እንደብርሃን ነጭ ሆነ ሙሴና ኤልያስም ከእርሱ ጋር ሲነጋገሩ ታዩኣቸው ጴጥሮስም በዚህ መኖር ለእኛ መልካም ነው አለ አብም በብሩህ ደመና ሆኖ የምደወው ልጄ ይህነው እርሱን ስሙት አለ ደቀ መዛሙርቱም ሰምተው በፊታቸው ወደቁ እጅግም ፈርተው ነበርኢየሱስም ዳሶ ተነሱ አትፍሩም አላቸው ቀና ብለው ሲያዩም ከኢየሱስ በቀር ማንንም አላዩም። ቅዱስ ጴጥሮስ ጌታን አንድ ለአንተ አንድ ለሙሴ፣አንድ ለኤልያስ ዳስ ሠርተን በዚህ መኖር መልካም ነው ብሎ የተናገረለት ደብረ ታቦር የቤተ ክርስቲያን ምሳሌ ነውከብሉይ ኪዳን ቅዱሳን ሙሴና ኤልያስ ከሐዲስ ኪዳን ቅዱሳን ጴጥሮስ ያዕቆብና ዮሐንስ፣ከደናግል ኤልያስና ዮሐንስ ከሕጋውያን ሙሴና ጴጥሮስ ከጌታ ጋር መገኘታቸው ቤተክርስቲያን የእነዚህ ሁሉ ቅዱሳን ኅብረት መሆኗን ያሳያል በደብረ ታቦር ቅዱሳን እንደተገኙ ቤተክርስቲያም የምእመናን መገኛ ናት።በደብረ ታቦር የእግዚአብሔር ክብር እንደተገለፀ ቤተክርስቲያንም የእግዚአብሔር ክብር የሚገለፅባት ናት። ይሁዳ ወደብረ ታቦር ባለመውጣቱ ምሥጢር እንደተሠወረበት ወደቤተክርስቲያን የማይመጣ ምእመንም ከምሥጢራት የራቀ ይራቀ ይሆናል። ይሁዳን ከዚህ ኅብረት የለየ ኀጢአት እኛንም ኀጢአት ከቤተክርስቲያን ኅብረት እንዳይለየን! የምሕረት አምላክ ልዑል እግዚአብሔር በቸርነቱ ይጠብቀን። ሊቀ ማእምራን ሰሎሞን ፈጠነየጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከትየሊቃውንት ጉባኤ ዋና ሰብሳቢ
“የአትትዎ ለኀጥእ ከመኢይርአይ ስብሐተ እግዚአብሔር – የእግዚአብሔርን ክብር እንዳያይ ኀጢአተኛውን ሰው ያርቁታል”ኢሳ ፳፮፥፲ Read More »