በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት

Uncategorized

ሠላሳ ሦስት አዳዲስ አማንያን ተጠምቀው የሥላሴን ልጅነት አገኙ!

ኤክቱስ ሐምሌ 19/2018 ዓ.ም በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት በኮሬ ዞን ወረዳ ቤተ ክህነት በቆሬ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ሠላሳ ሶስት አዳዲስ አማንያን ተጠምቀው የሥላሴን ልጅነት አገኙ። በተያያዘ የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል (ሐምሌ ገብርኤል) በታላቅ ድምቀት መከበሩ ተገልጿል።

ሠላሳ ሦስት አዳዲስ አማንያን ተጠምቀው የሥላሴን ልጅነት አገኙ! Read More »

ብፁዕ አቡነ ገሪማ ለአስራ ስምንት ደቀ መዛሙርት ሥልጣነ ክህነት ሰጡ!

ኤክቱስ ሐምሌ 19/2018 ዓ.ም ብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል የሐምሌ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል በሚከበርበት በጪጩ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ተገኝተው ለ17 ደቀ መዛሙርት የዲቁና ለ1 ዲያቆን የቅስና በአጠቃላይ ለ18 ደቀመዛሙርት ሥልጣነ ክህነት ሰጥተዋል። ደቀ መዛሙርቱ ለዲቁና እና ለቅስና የሚያበቃቸውን መንፈሳዊ ትምህርት ሲከታተሉ የቆዩ ሲሆኑ ከመሾማቸው በፊትም ብቁ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ፈተና ተሰጥቷቸው ማለፋቸው ተገልጿል። ብፁዕነታቸው በሰጡት አባታዊ ቃለ ምዕዳን የተቀበሉት እጅግ ትልቅ ኃላፊነት መሆኑን አሳስበው አገልጋዮቹ መንጋውን በንጽሕና፣ በትጋትና በቅድስና እንዲጠብቁ አደራ ብለዋል።

ብፁዕ አቡነ ገሪማ ለአስራ ስምንት ደቀ መዛሙርት ሥልጣነ ክህነት ሰጡ! Read More »

በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል የሚከበርባቸው አብያተ ክርስቲያናት!

ኤክቱስ ሐምሌ 18/2018 ዓ.ም በዲላና ወናጎ ወረዳ ቤተ ክህነት በይርጋጨፌ ወረዳ ቤተ ክህነት በኮቾሬ ገደብና ጮርሶ ወረዳዎች ቤተ ክህነት በቡሌና ረጴ ወረዳዎች ቤተ ክህነት በኮሬ ዞን ወረዳ ቤተ ክህነት በቡርጂ ዞን ወረዳ ቤተ ክህነት “እነሆ እኔ የተፈቱ በእሳቱም መካከል የሚመላለሱ አራት ሰዎች አያለሁ ምንም አላቆሰላቸውም የአራተኛውም መልክ የአማልክትን ልጅ ይመስላል” ዳን ፫፥፺፩

በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል የሚከበርባቸው አብያተ ክርስቲያናት! Read More »

በከፍተኛ ውጤት የተመረቁ ተማሪዎች የተሸለሙት ዋንጫዎች በዐውደ ምሕረት ላይ ለሰንበት ትምህርት ቤታቸው አበረከቱ!

ኤክቱስ ሐምሌ 7/2018 ዓ.ም ​በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት በዲላና ወናጎ ወረዳ ቤተ ክህነት የዲላ መካነ ቅድስት ሥላሴ ወአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን የፍሬ ተዋሕዶ ሰንበት ትምህርት ቤት አባላት ከተማሩባቸው ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በከፍተኛ ማዕረግ መመረቃቸው ተበስሯል። ከተመራቂዎቹ መካከል ዘማሪት እስከዳር እሸቴ ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ በሜካኒካል ኢንጅነሪንግ የትምህርት ክፍል 3.98 በማምጣት የዋንጫ ተሸላሚና የማዕረግ ተመራቂ መሆን ችላለች። በተመሳሳይ ወጣት የምስራች ምትኩ ከዲላ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ በዲግሪ መርሃግብር 4.00 ሙሉ ነጥብ በማስመዝገብ ከግቢው ጠቅላላ አንደኛ በመሆን ባለ ሁለት ዋንጫ እና ባለ ሁለት የወርቅ ሜዳልያ ተሸላሚ ሆናለች። ​ዛሬ በተከበረው ዓመታዊው የሐምሌ ቅድስት ሥላሴ የንግሥ በዓል ላይ ወጣት የምስራች ምትኩ ያስመዘገበችውን ታላቅ ስኬት ተከትሎ ያገኘችውን የክብር ሽልማት ይዛ ቀርባለች። ለዚህ ማዕረግ ላበቃ ለእግዚአብሔር አምላክ ምስጋናዋን ካቀረበች በኋላ በዕለቱ ዐውደ ምሕረት ላይ የተሸለመችውን የክብር ዋንጫ ለዓመታት በእምነትና በአገልግሎት ኮትኩቶ ላሳደጋት ለፍሬ ተዋሕዶ ሰንበት ትምህርት ቤት በአደባባይ በአደራነት አስረክባለች። ​በዕለቱ በዐውደ ምሕረቱ ላይ የተከናወነው ይህ ሥነ ሥርዓት በበዓሉ ላይ በታደሙት አገልጋዮችና ምዕመናን ዘንድ መንፈሳዊ ኩራትን የፈጠረ ነበር። ይህም ወጣቶች በመንፈሳዊ አገልግሎታቸው እየጠነከሩ በዓለማዊ ትምህርታቸውና በሳይንሱ ዘርፍም ከፍተኛ ውጤት ማምጣት እንደሚችሉ በተግባር ያሳየ አርአያ ሆኖ አልፏል።

በከፍተኛ ውጤት የተመረቁ ተማሪዎች የተሸለሙት ዋንጫዎች በዐውደ ምሕረት ላይ ለሰንበት ትምህርት ቤታቸው አበረከቱ! Read More »

ሃያ ስድስት አዳዲስ አማንያን ተጠምቀው የሥላሴን ልጅነት አገኙ!

ኤክቱስ ሐምሌ 7/2018 ዓ.ም በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት በኮሬ ዞን ወረዳ ቤተ ክህነት በከረዳ ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ሃያ ስድስት አዳዲስ አማንያን ተጠምቀው የሥላሴን ልጅነት አገኙ። በተያያዘ የቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ በዓል (ሐምሌ ሥላሴ) በታላቅ ድምቀት መከበሩ ተገልጿል።

ሃያ ስድስት አዳዲስ አማንያን ተጠምቀው የሥላሴን ልጅነት አገኙ! Read More »

የጨለለቅቱ ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ቅዳሴ ቤቱ እና የሐምሌ ሥላሴ ዓመታዊ በዓል ብፁዕነታቸው በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተከበረ!

ኤክቱስ ሐምሌ 7/2018 ዓ.ም በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት በኮቾሬ፣ ገደብና ጮርሶ ወረዳዎች ቤተ ክህነት በጨለለቅቱ ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ብፁዕ አቡነ ገሪማ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል በተገኙበት ተከብሯል። ታቦቱ ከመንበሩ ከወጣ በኋላ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ያሬዳዊ ዝማሬ ያቀረቡ ሲሆን የደብሩ የሰንበት ትምህርት ቤት ዘማርያንም ዝማሬ አቅርበዋል። የዕለቱን ትምህርት ያስተማሩት መምህር እስራኤል ሲሆን በዓሉ የሚከበርበትን ምክንያት በሚገባ በመዘርዘር ወደ ሕይወት እየቀየሩ በሚገባ አስተምረዋል። በደብሩ ለሚሠሩ የልማት ሥራዎች የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃግብር ያከናወኑት መልአከ ሰላም እኔምአየሁ ዓለሙ የወረዳ ቤተ ክህነቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ናቸው። በመቀጠል በደብሩ አስተዳዳሪ በበኩረ ትጉሃን አእምሮ ሙሉ አቅራቢነት ለሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ግንባታ አስተዋጽዖ ላደረጉ አካላት በብፁዕነታቸው የምስጋና የምስክር ወረቀትና ሽልማት ተበርክቷል። በመጨረሻም በመልአከ ሰላም ቆሞስ አባ ዮሐንስ ምሕረቱ የሀገረ ስብከቱ የመንፈሳዊ ትምህርትና የካህናት አገልግሎት ክፍል ኃላፊ ጋባዥነት ብፁዕነታቸው በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በጌዴኡፋ ቋንቋዎች መዝሙር የዘመሩ ሲሆን አክለውም ስለቤተ ክርስቲያን ምንነት በማንሳት ካስረዱ በኋላ የሰው ልጅ ሰውነት የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንደመሆኑ ራሱን እንዴት ከእርኩሰት መጠበቅ እንዳለበት አባታዊ መመሪያ ሰጥተው በጸሎት ፈጽመዋል።

የጨለለቅቱ ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ቅዳሴ ቤቱ እና የሐምሌ ሥላሴ ዓመታዊ በዓል ብፁዕነታቸው በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተከበረ! Read More »

አስራ ስድስት አዳዲስ አማንያን በብፁዕ አቡነ ገሪማ ተጠምቀው የሥላሴን ልጅነት አገኙ!

ኤክቱስ ሐምሌ 7/2018 ዓ.ም በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት በኮቾሬ፣ ገደብና ጮርሶ ወረዳዎች የሚገኙ በጨለለቅቱ ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን አስራ ስድስት አዳዲስ አማንያን በብፁዕ አቡነ ገሪማ ተጠምቀው የሥላሴን ልጅነት አግኝተዋል። ከተጠማቅያኑ መካከል አስራ ሁለቱ በጨለለቅቱ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ አማካኝነት፣ ቀሪዎቹ አራት አዳዲስ አማንያን ደግሞ በማኅበረ ቅዱሳን ጨለለቅቱ ማዕከል አማካኝነት የቅድመ ጥምቀት ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ መሆናቸው ተገልጿል። ይህ መንፈሳዊ አገልግሎት በብፁዕነታቸው መመሪያ ሰጪነት በሀገረ ስብከቱ ሥር በሚገኙ አድባራት የሚከናወነውን የክርስቶስን የመንግሥቱን ወንጌል የማስፋፋት ሥራ ውጤት መሆኑ የተገለጸ ሲሆን መሰል የማስተማርና የማጥመቅ አገልግሎቶች በቀጣይም ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተመልክቷል።

አስራ ስድስት አዳዲስ አማንያን በብፁዕ አቡነ ገሪማ ተጠምቀው የሥላሴን ልጅነት አገኙ! Read More »

ስምንት አዳዲስ አማንያን ተጠምቀው የሥላሴን ልጅነት አገኙ!

ኤክቱስ ሐምሌ 6/2018 ዓ.ም በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት በዲላና ወናጎ ወረዳ ቤተ ክህነት በሻራ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ከዚህ ቀደም የሌላ ቤተ እምነት ተከታዮች የነበሩ ስምንት አዳዲስ አማንያን ተጠምቀው የሥላሴን ልጅነት አግኝተዋል።

ስምንት አዳዲስ አማንያን ተጠምቀው የሥላሴን ልጅነት አገኙ! Read More »

በጨለለቅቱ ከተማ የተገነባው የቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ገሪማ ቡራኬ ተከናነ!!

ኤክቱስ ሐምሌ 6/2018 ዓ.ም በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት በኮቾሬ፣ ገደብና ጮርሶ ወረዳዎች ቤተ ክህነት በጨለለቅቱ ከተማ ሲገነባ የቆየው የቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ሕንጻ ግንባታ ተጠናቆ በብፁዕ አቡነ ገሪማ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ተባረከ። በመርሃግብሩ መልአከ ሰላም ቆሞስ አባ ዮሐንስ ምሕረቱ የሀገረ ስብከቱ የመንፈሳዊ ትምህርትና የካህናት አገልግሎት ክፍል ኃላፊ፣ የወረዳ ቤተ ክህነቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ሰላም እኔምአየሁ ዓለሙ፣ የወረዳ ቤተ ክህነቱ ዋና ጸሐፊ በኩረ ትጉሃን አስቻለው ገብረ መድኅን፣ በኩረ ትጉሃን አእምሮ ሙሉ የሁለቱ አድባራት አስተዳዳሪ ፣ ካህናትና ዲያቆናት እንዲሁም በርካታ የአካባቢው ምዕመናን በሥነ ሥርዓቱ ላይ በመገኘት የበረከቱ ተካፋይ ሆነዋል። ይህ አዲስ የቤተ ክርስቲያን ሕንጻ መመረቅ በአካባቢው ያለውን የወንጌል አገልግሎት ይበልጥ ለማስፋፋት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ተገልጿል።

በጨለለቅቱ ከተማ የተገነባው የቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ገሪማ ቡራኬ ተከናነ!! Read More »

የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ለዲላ ዋለሜ ሰዓሊተ ምሕረት ኪዳነ ምሕረት፣ ለወናጎ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም እና ለጨለለቅቱ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም አብያተ ክርስቲያናት የመጽሐፍ መምህራንን ለመቅጠር ባወጣው ማስታወቂያ መሠረት መስፈርቱን አሟልተው የተገኙ እጩ(ዎች) ያመጡት አጠቃላይ የፈተና ውጤት!

ኤክቱስ ሐምሌ 6/2018 ዓ.ም

የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ለዲላ ዋለሜ ሰዓሊተ ምሕረት ኪዳነ ምሕረት፣ ለወናጎ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም እና ለጨለለቅቱ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም አብያተ ክርስቲያናት የመጽሐፍ መምህራንን ለመቅጠር ባወጣው ማስታወቂያ መሠረት መስፈርቱን አሟልተው የተገኙ እጩ(ዎች) ያመጡት አጠቃላይ የፈተና ውጤት! Read More »

Scroll to Top