በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት

July 2025

19 ነፍሳት የሥላሴን ልጅነት አገኙ!!

በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት በኮሬ ወረዳ ቤተክህነት ሥር በሚገኘው በኬረዳ ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ሐምሌ7/2017 ዓ.ም በቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል ላይ 19 ኢአማንያን ተጠምቀው የሥላሴ ልጅነትን አግኝተዋል ። ኤክቱስ ሐምሌ 8/2017 ዓ.ም

19 ነፍሳት የሥላሴን ልጅነት አገኙ!! Read More »

የቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል በዲላ መካነ ቅድስት ሥላሴ ወአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን በታላቅ መንፈሳዊ ድምቀትና ክብር ተከበረ!!

በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት በመንበረ ጵጵስና ወናጎ ወረዳ ቤተክህነት ሥር በሚገኘው በዲላ መካነ ቅድስት ሥላሴ ወአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን ብፁዕ አቡነ ገሪማ የሀገረ ስብከቱ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል በተገኙበት ተከበረ። በዕለቱም የሀገረ ስብከቱ የስብከተ ወንጌል ክፍል ኃላፊ ሊቀትጉሃን ቀሲስ ሀብታሙ አበበ ፣የመንበረ ጵጵስና ወናጎ ወረዳ ቤተክህነት ሊቀጠበብት መሪጌታ መሠረት ይልማ፣የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ሰላም አምሳሉ ሣለ ፣ለመንፈሳዊ ጉባኤ የተጋበዙ ሊቀ ሊቃውንት ዮሴፍ ፣መጋቤ ሐዲስ አድነው ወንድሙ ፣ዘማሪያን፣ የአድባራት አስተዳዳሪዎች ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን የዲላና አካባቢው ምዕመናን በተገኙበት ተከብሯል። መርሐ ግብሩ በሀገረ ስብከቱ ስብከተ ወንጌል ክፍል የተመራ ሲሆን የመጀመሪያውን ክፍለ ጊዜ ያስተማሩት መጋቤ ሐዲስ አድነው ወንድሙ ሲሆኑ ታቦቱ ከመንበረ ክብሩ ከወጣ በኋላ በደብሩ ፍሬ ተዋህዶ ሰንበት ት/ቤት መዘምራን ወረብ ከቀረበ በኋላ ሁለተኛውን ትምህርት የሰጡት ሊቀ ሊቃውንት ዮሴፍ ሲሆኑ በመቀጠል ለቤተክርስቲያኑ የልማት ሥራ የማስተባበር በመጋቤ ሐዲስ አድነው ወንድሙ ተከናውኗል ። በመጨረሻም በብፁዕ አቡነ ገሪማ የሀገረ ስብከቱ ጳጳስ ቃለ ምዕዳንና ጸሎት ተደርጎ በዓሉ ፍጻሜውን አግኝቷል ። ኤክቱስ ሐምሌ 7/2017 ዓ.ም

የቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል በዲላ መካነ ቅድስት ሥላሴ ወአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን በታላቅ መንፈሳዊ ድምቀትና ክብር ተከበረ!! Read More »

የዘማሪ አዲስ ነጋሽ ቁጥር አንድ የዝማሬ አልበም ተመረቀ!!

በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት በመንበረ ጵጵስና ወናጎ ወረዳ ቤተክህነት ሥር በምትገኘው በጌ/ሰ/ባዕታ ለማርያም ቤተክርስቲያን በሰንበት ት/ቤት አገልጋይነት እንዲሁም በሀገረ ስብከቱ በሚገኙ አድባራትና አብያተ ክርስቲያናት በዝማሬ የሚያገለግለው ዘማሪ አዲስ ነጋሽ የሀገረ ስብከቱ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ገሪማ እና የሀገረ ስብከቱ የየክፍል ኃላፊዎች በተገኙበት ካህናት የዲላ ምዕመናን በተገኙበት በዲላ ዋለሜ ደብረ ሰላም ቅዱስ ዑራኤል ቤተክርስቲያን አዳራሽ በብፁዕ አቡነ ገሪማ የዘማሪ አዲስ ነጋሽ የዝማሬ አልበም በብፁዕነታቸው ተመርቋል። በዕለቱም በተለያዩ ዘማሪያን ዝማሬ ፣በብፁዕ አቡነ ገሪማ የሀገረ ስብከቱ ጳጳስ ትምህርተ ወንጌል ፣የዝማሬ አልበሙ ምርቃት ፣ስጦታና ጨረታ ተከናውኖ በመርሐ ግብሩ በጸሎት ተዘግቷል ። ኤክቱስ ሐምሌ 6/2017 ዓ.ም

የዘማሪ አዲስ ነጋሽ ቁጥር አንድ የዝማሬ አልበም ተመረቀ!! Read More »

የሀዋሳ ታቦር ፍኖተ ጥበብ መንፈሳዊ ኮሌጅ ለሦስት ዓመታት ያስተማራቸውን ደቀ መዛሙርት ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ እና የቅዱስ ሲኖስ ዋና ጸሐፊው በተገኙበት አስመረቀ።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የታቦር ፍኖተ ጥበብ መንፈሳዊ ኮሌጅ ፲፭ ደቀ መዛሙርትን ቅዳሜ ሐምሌ ፭ ቀን ፳፻ ፲ወ፯ዓ/ም ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትየ፣የጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያ ኃላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ለመጀመሪያ ጊዌ በደማቅ ሥነሥርዓት አስመርቋል። ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የሲዳማ ሀገረ ስብከትና የሀዋሳ ታቦር ፍኖተ ጥበብ መንፈሳዊ ኮሌጅ ሊቀ ጳጳስ በዚሁ የምረቃ ሥነሥርዓት ላይ ባስተላለፉት አባታዊ መልዕክት በዛሬው ዕለት የተመረቃችሁ ደቀ መዛሙርት በምትሰማሩበት ሁሉ ማስተዋልና ጥበብን በመከተል ወደ ዓለም ዳስቻ ሁሉ ሂዱ ወንጌልንም ስበኩ የሚለውን የወንጌሉን ቃል በመከተልና በመተግበር እንድታገለግሉ አደራ በማለት አገልግሎታችሁ ሁሉ ውጤታማና የተሳካ ይሆን ዘንድ አምላካችን እግዚአብሔርን እንለምናለን ብለዋል። በማያያዝም ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያናችን ይህንን የትምህርት እድል እንዲመቻች ያደረገችው ዶግማ፣ቀኖናዋና ትውፊቷ ተጠብቆ ለተተኪው ትውልድ ይተላለፍ ዘንድ ነው። ያሉት ብፁዕነታቸው ዛሬ ለምረቃ የበቃችሁ ደቀ መዛሙርትም ይህንን ታላቅ ኃላፊነት ለመወጣት መዘጋጀትና በየትኛውም ስፍራና ሁኔታ ውስጥ ሁሉ የሚጠበቅባችሁን ሁሉ ለመወጣት የተዘጋጃችሁ መሆን ይኖርባችኋል። ብለዋል። ወደ ኮሌጃችን ለመማር ስትመጡ የገባችሁትን ቃል እንዲሁም ዛሬም በዚህ የምረቃ መርሐ ግብር ቤተክርስቲያንን እና ሕዝብን በቅንነትና በታማኝነት ለማገልገል የገባችሁት ቃል ኪዳን ባገኛችሁት ዕውቀትና ክህሎት በትጋት እንደ ምትፈጽሙት እምነታችን ጽኑዕ ነው።ያሉት ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የኮሌጃችን የመጀመሪያ ምሩቃን ደቀ መዛሙርት ልጆቻችን! በሥራችሁ ሁሉ የምታሳዩት ጥረትና ትጋት እንዲሁም ለሁሉ አርዓያና ምሳሌ በመሆን በምትሰጡት አገልግሎት ቤተ ክርስቲያንን እና የተማራችሁበትን ኮሌጅ የምታስመሰግኑ እንደ ምትሆኑ እምነታችን ነው። መጪው የሥራና የአገልግሎት ዘመናችሁ ሁሉ የተቃና እንዲሆን ዘወትር ጸሎታችን ነው በማለት መልዕክታቸውን አጠናቀዋል። በምረቃ ሥነሥርዓቱ ላይ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የተመራቂ ደቀ መዛሙርት ቤተሰቦች ተገኝተዋል። በኮሌጁ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩትና በዛሬው ዕለት ለምረቃ የበቁት ደቀ መዛሙርት በሲዳምኛ፣በኦሮምኛ፣በዳውሮኛ፣ በከምባትኛ፣በሃድይኛ፣በጋሞኛ፣በኮይሬኛ፣በጌዲኦኛ፣በከፋኛና በወላይትኛ ቋንቋዎች ማስተማር የሚችሉ በመሆናቸው በቤተክርስቲያን አገልግሎት ዙሪያ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክቱ ይታመናል። በመጨረሻም ብፁዕ አቡነ ጎርጎሬዎስ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ለተመራቂ ደቀ መዛሙርት የእንኳን ደስ አላችሁ አባታዊ መልዕክት አስተላልፈው መርሐ ግብሩ በጸሎት ተጠናቋል። ©የኢኦተቤክ ህዝብ ግንኙነት

የሀዋሳ ታቦር ፍኖተ ጥበብ መንፈሳዊ ኮሌጅ ለሦስት ዓመታት ያስተማራቸውን ደቀ መዛሙርት ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ እና የቅዱስ ሲኖስ ዋና ጸሐፊው በተገኙበት አስመረቀ። Read More »

ብፁዕ አቡነ ገሪማ በዲላ ደብረ ሰላም ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን ያደረጉት የመስክ ጉብኝት!!

በባለፈው ዓመት ብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል እያንዳንዱ መሬት ጾም ማደር እንደሌለበት ባስተላለፉት መመሪያ መሰረት በሀገረ ስብከቱ ባሉ አጥብያ አቢያተ ክርስቲያናት የተሰሩ በርካታ የግብርና የልማት ሥራዎት እየተጎበኙ ይገኛሉ። በዚሁ መሰረት የዲላ ደብረ ሰላም ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን አንድ ሄክታር በላይ በሚሆን መሬት ላይ ፓፓያ ፣ ማንጎ፣ የጓሮ አትክልት ፣ ብርቱካን፣ ሸንኮራ እና የንብ እርባታ ተጎብኝቷል። ኤክቱስ ሐምሌ 04/2017

ብፁዕ አቡነ ገሪማ በዲላ ደብረ ሰላም ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን ያደረጉት የመስክ ጉብኝት!! Read More »

በ አረጋዊዉ አባት ርዕሠ ደብር ለገሠ በለጠ አስተባባሪነት ለገጠር አብያተክርስቲያናት የንዋየ ቅድሳትና የቅዱሳት መጽሐፍት ድጋፍ ተደረገ !!

በጌዴኦ በኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት በዲላ ደብረ ገነት ለብዙ ዓመታት ያገለገሉትና አሁን በመንፈሳዊ አገልግሎት ላይ የሚገኙት ርዕሰ ደብር ለገሠ በለጠ የንሰሐ ልጆቻቸውን በማስተባበር በሀገረ ስብከቱ ለሚገኙ በንዋየ ቅድሳት አለመኖር ምክንያት አገልግሎት ለማይሰጡ አብያተክርስቲያን የሚሆን ንዋየ ቅድሳት ቅዱሳትና መጽሐፍትን ለብፁዕ አቡነ ገሪማ ለሀገረ ስብከቱ ጳጳስ አስረክበዋል ። በተለይ ርዕሰ ደብር ለገሰ በለጠ ድጋፍ የተደረጉትን መጽሐፍቱን በግል ገንዘባቸው እንዳስደጎሱ ታውቋል። ድጋፍ የተደረጉ የንዋየ ቅድሳት አይነት፦ ፩. የአምስት ሰሞነኛ ሙሉ ልብሰ ተክህኖ ፪. ወንጌል አዲስ ኪዳን በግዕዝ እና በአማርኛ-ተአምረ ማርያም-መጽሐፈ ቅዳሴ በግዕዝና በአማርኛ -መዝሙረ ዳዊት-መጽሐፈ ሰዓታት-ማህሌተ ጽጌ-ፀሎተ ዕጣን-መጽሐፈ ግጻዌ-መጽሐፈ ግንዘት-መጽሐፈ ክርስትና ሲሆን ይህን የንዋየ ቅድሳትና የመጽሐፍት ስጦታ ያበረከቱት ወልደ ሚካኤል፣ ኅይለ ገብርኤል፣ወልደ ገብርኤል ፣ ወልደ አረጋዊ፣ ፍቅረ አማኑኤል፣ ኃይለ ማሪያም ናቸው። ብፁዕ አቡነ ገሪማ የሀገረ ስብከቱ ጳጳስ የተበረከቱትን ንዋየ ቅድሳትና የመጽሐፍት ስጦታ ተረክበው መልዕክት ምስጋና አረጋዊ አባት ርዕሰ ደብር ለገሰ በለጠንና በገንዘባቸው የተባበሩትን ሁሉ አመስግነዋል ። ኤክቱስ ሐምሌ 1/2017 ዓ.ም

በ አረጋዊዉ አባት ርዕሠ ደብር ለገሠ በለጠ አስተባባሪነት ለገጠር አብያተክርስቲያናት የንዋየ ቅድሳትና የቅዱሳት መጽሐፍት ድጋፍ ተደረገ !! Read More »

የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ዓመታዊ የልደት በዓል በወናጎ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያን በታላቅ ድምቀት ተከበረ!!

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በየዓመቱ ሰኔ ፴ ቀን በታላቅ መንፈሳዊ ክብር የሚከበረው ዓመታዊ የቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ የልደት በዓል በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት በመንበረ ጵጵስናና ወናጎ ወረዳ ቤተክህነት የሀገረ ስብከቱ ስብከተ ወንጌል ክፍል ኃላፊ ሊቀትጉሃን ቀሲስ ሀብታሙ አበበ የመንበረ ጵጵስናና ወናጎ ወረዳ ቤተክህነት ዋና ጸሐፊ ሊቀኅሩያን ቀሲስ እሸቱ ዋለ የወናጎ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያምና ቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን ዋና አስተዳዳሪ መልአከ ጽዮን ግሩም በቀለ ሊቃውንት ካህናትና የወናጎና የአካባቢው ምዕመናን በተገኙበት በወናጎ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያን ተከብረ። መርሃግብሩ በደብሩ ዋና ጸሐፊ በሊቀ ስዩማን ቀሲስ ምሕረቴ ገብረ ሥላሴ የተመራ ሲሆን ለዕለቱ የሚስማማ ወረብ በደብሩ ሰንበት ትምህርት ቤት አባላት ቀርቧል። ትምህርተ ወንጌል የመንበረ ጵጵስናና ወናጎ ወረዳ ቤተ ክህነት ዋና ጸሐፊ ሊቀ ኅሩያን እሸቱ ዋለ የሰጡ ሲሆን በዕድሳት ላይ ለሚገኘው ለደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃግብር በሀገረ ስብከቱ ስብከተ ወንጌል ክፍል ኃላፊ በሊቀ ትጉሃን ሀብታሙ አበበ ተሰጥቶ መርሃግብሩ በጸሎት ተፈጽሟል። ኤክቱስ ሰኔ 30/2017

የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ዓመታዊ የልደት በዓል በወናጎ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያን በታላቅ ድምቀት ተከበረ!! Read More »

የወልቂጤ ቅዱስ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ለ 3 ተከታታይ ዓመታት ሲያስተምራቸው የነበሩ ደቀ መዛሙርትን አስመረቀ።

የወልቂጤ ቅዱስ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ለተከታታይ 3 ዓመታት ሲያስተምራቸው የነበሩ 22 ደቀ መዛሙርትን በዲፕሎማ እንዲሁም ለአንድ ወር ሲሰለጥኑ የነበሩ 38 ካህናትን በሰርተፊኬት በዛሬው ዕለት አስመርቋል። በምርቃት መርሐ ግብሩ ላይጨብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ የኮሌጁ መሥራችና የበላይ ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ገዳማት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የሲዳማ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት የደቡብ ኦሞ እና አሪ ዞኖች ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ የአማሮ እና ቡርጂ ዞኖች ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ፕሮፌሰር አባ ኃይለ ገብርኤል የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ምክትል ፕሬዚዳንት ፣ የሀገረ ስብከቱ የሥራ ኃላፊዎች ፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ፣ የተመራቂ ተማሪዎች ቤተሰቦች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። ተመራቂ ደቀ መዛሙርቱ ከምርቃት መርሐ ግብሩ በፊት በብፁዕ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ተቀብለዋል። ሰኔ ፳፱/፳፻፲፯ ዓ/ም ኤክቱስ ©ሳሌም የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

የወልቂጤ ቅዱስ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ለ 3 ተከታታይ ዓመታት ሲያስተምራቸው የነበሩ ደቀ መዛሙርትን አስመረቀ። Read More »

“ምእመናን በሃይማኖት እንዲጸኑ ሰላምን፣ፍቅርን እና አንድነትን ስበኩ!” ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ

በዛሬው ዕለት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳም የበላይ ኃላፊ፣ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣የደቡብ ምሥራቅ ትግራይና የራያ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ብፁዕ አቡነ ሕዝቄል የከፋና ሸካ፣ቤንች ሸኮ እና ምዕራብ ኦሞ አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስና የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ኀላፊ እና ሌሎች ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እግዶች በተገኙበት የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ በትርጓሜ መጻሕፍትና በነገረ መለኮት የትምህርት ዘርፍ በቀን እና በማታ ያስተማራቸውን 769 ደቀ መዛሙርትን አስመርቋል። ቅዱስነታቸው ባስተላለፉት መልእክት ምእመናን ትእዛዘ እግዚአብሔርን እንዲጠብቁ፣በምግባር እንዲጎለብቱና በሃይማኖት እንዲጸኑ ሰላምን፣ፍቅርን እና አንድነትን በመስበክ የማስተማር ኃላፊነታችሁን ተወጡ ሲሉ ተመራቂዎችን አሳስበዋል፡፡ አክለውም ጌታችን ሐዋርያትን ሂዱና አስተምሩ ብሎ እንደላካቸው ሁሉ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ይህንን መሠረት አድርጋ በየዓመቱ ተማሪዎችን እያስመረቀች ትገኛለች ያሉ ሲሆን ሰላም ከሌለ ምንም አይኖርም ስለዚህም መቻቻል እንዲኖር፣አንድነት እንዲሰፍን እንዲሁም የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ግብ እንዲሳካ ድርሻችሁን መወጣት ይጠበቅባችኋል ብለዋል፡፡ የኮሌጁ የበላይ ኀላፊ ብፁዕ አቡነ ሕዝቄል በበኩላቸው ነፍስን እና ሥጋን የሚጠግን፣የሚያለመልምና የሕይወት ውኃ ትምህርት በመሆኑ ደቀ መዛሙርቱ በተማሩት ትምህርት መሠረት በሚሄዱበት ሁሉ የዓለሙን ፈተና ተቋቁመው ቤተ ክርስቲያንን ማገልገል እንዳለባቸው ተናግረዋል። በምርቃት መርሐ ግብሩ ላይ በተመራቂዎች ወረብና ቅኔ የቀረበ ሲሆን ከፍተኛ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡ የሰዋስወ ብርሃን ቅዱ ስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ከፍተኛ መንፈሳዊ ትምህርት ቤት በሚል ስያሜ የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንትንና መምህራንን ማሠልጠኛ እንዲሆን በ1930 ዓ.ም ተመሥርቶ በአሁኑ ወቅት ከ82 ዓመታት በላይ ሆኖታል፡፡

“ምእመናን በሃይማኖት እንዲጸኑ ሰላምን፣ፍቅርን እና አንድነትን ስበኩ!” ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ Read More »

Scroll to Top