በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት

ቀዳሚ ገጽ ዜና

ከአራቱ ወረዳ ለተውጣጡ ከቋንቋ ሰባኪያነ ወንጌል ጋር ውይይት ተደረገ!!

ከአራቱ ወረዳ ለተውጣጡ ከቋንቋ ሰባኪያነ ወንጌል ጋር ውይይት ተደረገ!! በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ከአራት ወረዳ ቤተክህነት ማለትም ከመንበረ ጵጵስናና ወናጎ፣ ከይርጋጨፌ፣ከኮቸሬና ገደብ ፣ከቡሌና ረጴ ወረዳዎች ከተውጣጡ በጌዴኡፋ ቋንቋ የስብከተ ወንጌል አገልግሎት ከሚሰጡ ሰባኪያነ ወንጌል ጋር ብፁዕ አቡነ ገሪማ የሀገረ ስብከቱ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ጋር ውይይት ተደረገ። ውይይቱ ከቤተክርስቲያን ካህናት ማሰልጠኛ ተመርቀው ወጥተው ምን አከናወኑ፣የስብከተ ወንጌል አገልግሎት ሲሰጡ የገጠማቸው ተግዳድሮት ነበረ፣ለገጠማቸው ችግር የወሰዱት የመፍትሔ ሃሳብ ምን ነበር፣በአገልግሎት የተገኘው ውጤት ምን ነበር፣ያሉትን ለማጽናት የጠፉትን ለመመለስ አዳዲስ ኢአማንያንን ለማምጣት ምን አከናወኑ በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን። ሰባኪያነ ወንጌሉ በአገልግሎት ላይ የገጠማቸውን ችግር ያነሱ ሲሆን መስዋዕትነት እስኪከፍሉ ድረስ ዋጋ መክፈላቸው ሰንበት ት/ቤት ማደራጀት ባዕድ አምልኮ ማጥፋት ብዙ ኢአማኒያን ማስጠመቅ ኮርስ መስጠት በማኀበራዊ ሕይወት መሳተፍ በሀዘንና በደስታ ስብከተ ወንጌል መስጠት የሚሉ የአገልግሎት ተግባራትን የዘረዘሩ ሲሆን። በቀጣይ ከተከናወነው ያልተሰራው ስለሚበዛ በቁጭት በቋንቋ ለማስተማር ቃል ገብተዋል። የሀገረ ስብከቱ ስብከተ ወንጌል ክፍል ኃላፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ሀብታሙ አበበ በሰጡት አስተያየት ለተጠራንበት አገልግሎት ቁርጠኛ መሆን እንደሚገባ ከጠባቂነት መውጣትና በዕቅድና በዓላማ ማገልገል አገልግሎታቸው ሁሉ በውጤት የታጀበ መሆን እንዳለት በተለይ ያሉትን በማጽናትና መጠበቅ የጠፉትን ማምጣት አዳዲስ አማኒያንን ወደ ክርስትና በማምጣት ላይ አገልግሎታቸውን መወጣት እንዳለባቸው አንስተዋል። በመጨረሻም በብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል በማጠቃለያው የስብከተ ወንጌል በሚገባ አገልግሎት አልተፈጸም የቤተክርስቲያንን ተልዕኮ በአግባቡ አውቆ ያለመፈጸም ሰባኪ ከጠባቂነት መውጣት ለዚህ አገልግሎት የተጠራን ባለዕዳዎች መሆንናችንን አንስተው የማሳመኑን የማስተማሩን ሥራ በአግባቡ መወጣት አለብን ብለዋል። በየመንደሩ የስብከተ ወንጌል ኬላ ማቋቋምና አገልግሎትን መፈጸም በማኀበራዊ ሁነቶች ላይ መሳተፍ በቁርጠኝነት ወንጌልን ማገልገል እንደሚያስፈልግ እስከ ሕይወት መስዋዕትነት መክፈል እንደሚገባ አሳስበው በቀጣይ ለአንድ ዓመት የሚቆይ ፕሮጀክት የተወጋጀና የስብከተ ወንጌል አገልግሎት ሥምሪት እንደሚሰጥ በማሳሰብ ውይይቱ ተጠናቋል ።

ከአራቱ ወረዳ ለተውጣጡ ከቋንቋ ሰባኪያነ ወንጌል ጋር ውይይት ተደረገ!! Read More »

በዲላ መዝገበ ምሕረት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን የተዘጋጀው ሁለተኛ ቀን መንፈሳዊ ጉባኤ ተጠናቀቀ።

በዲላ መዝገበ ምሕረት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን የተዘጋጀው ሁለተኛ ቀን መንፈሳዊ ጉባኤ ተጠናቀቀ። በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት በመንበረ ጵጵስናና ወናጎ ወረዳ ቤተ ክህነት በመዝገበ ምሕረት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን በዓለ ጽንሰት በማስመልከት የተዘጋጀው መንፈሳዊ ጉባኤ ሁለተኛ ቀን ተጠናቋል። በጉባኤው የሀገረ ስብከቱ ስብከተ ወንጌል ክፍል ኃላፊ ሊቀ ትጉሃን ሀብታሙ አበበ፣ የወረዳ ቤተ ክህነቱ ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ጠበብት መሪጌታ መሰረት ይልማ፣ የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ምሕረት ቀሲስ ሰናይ፣ ሰባኪያነ ወንጌል እና ዘማሪያን፣ የደብሩ ካህናትና ዲያቆናት፣ በርካታ ምዕመናን ተገኝተዋል። በጉባኤው የበገና ዝማሬ፣ ትምህርተ ወንጌል በተጋባዥ መምህራን፣ ዝማሬ የተሰጠ ሲሆን ጉባኤው ዛሬም እንደሚቀጥል ተገልጾ የመርሃግብሩ ፍጻሜ ሆኗል።

በዲላ መዝገበ ምሕረት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን የተዘጋጀው ሁለተኛ ቀን መንፈሳዊ ጉባኤ ተጠናቀቀ። Read More »

በሐሩ እግዚአብሔር ወልድ ቤተክርስቲያን በዓለ ጽንሰት በመንፈሳዊ ክብር ተከበረ።

በሐሩ እግዚአብሔር ወልድ ቤተክርስቲያን በዓለ ጽንሰት በመንፈሳዊ ክብር ተከበረ። በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት በይርጋጨፌ ወረዳ ቤተክህነት ሥር የሚገኘው በሐሩ እግዚአብሔር ወልድ ቤተክርስቲያን የጽንሰት በዓል የይርጋጨፌ ወረዳ ቤተክህነት ዋና ፀሐፊ መጋቤ ሃይማኖት ቀሲስ ብዙአየሁ ዳመና የደብሩ አስተዳዳሪ ካህናትና የሐሩና የአካባቢው ምዕመናንን በተገኙበት በታላቅ መንፈሳዊ ክብር ተከበረ። በዕለቱም ይርጋጨፌ ወረዳ ቤተክህነት ዋና ፀሐፊ መጋቤ ሃይማኖት ቀሲስ ብዙአየሁ ዳመና ለዕለቱ የሚስማማ የጌታን ዓለምን ለማዳን ከቅድስት ድንግል ማርያም በመንፈስ ቅዱስ ግብር በቅዱስ ገብርኤል ብስራት መጸነሱን ዓለምን ለማዳን የተጠቀመውን የፍቅር ጥበብ በሰፊው በመግለጽ አስተምረዋል። በመጨረሻም ለቤተክርስቲያኑ የልማት ሥራ የገቢ ማስገኛ ሥራ ምዕመናንን በማስተባበር ከተከናወነ በኋላ ጸሎትና ቡራኬ ተሰጥቶ የበዓሉ ፍጻሜ ሆኗል።

በሐሩ እግዚአብሔር ወልድ ቤተክርስቲያን በዓለ ጽንሰት በመንፈሳዊ ክብር ተከበረ። Read More »

ለሁለት ቀን የሚቆይ ሥልጠና ተጀመረ!!

ለሁለት ቀን የሚቆይ ሥልጠና ተጀመረ!! በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ለሀገረ ስብከቱ ሠራተኞች ከሀገረ ስብከቱ ከሁሉም ወረዳ ቤተክህነት እንዲሁም አድባራት ለተወከሉ ሥራአስኪያጅና አስተዳዳሪዎች ካህናት የአስተዳደር ሠራተኞች ለሁለት ቀን የሚቆይ ሥልጠና በሀገረ ስብከቱ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ገሪማ በተገኙበት በዲላ ዋለሜ ደብረ ሰላም ቅዱስ ዑራኤል ቤተክርስቲያን አዳራሽ በጸሎት ተጀመረ። ሥልጠናውን የሚሰጡት የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ ምክትል ፕሬዝዳት ፕሮፌሰር አባ ኃይለ ገብርኤል ሲሆኑ ሥልጠናውን ሰልጣኞች በቡድን ውይይት እንዲሳተፉና የውይይቱን ውጤት ለተሳታፊ እንዲያቀርቡ በማድረግ በርዕሰ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ በመስጠት ነው። #ሥልጠናው በኦርቶዶክሳዊ አገልግሎት ዙሪያ የተሰጠ ሲሆን ልዩ ልዩ አስረጂዎችን ከቡሉይ እና ሀዲስ ኪዳን በማቅረብ የቅዱሳን አባቶችን መጽሐፍት በዋቢነት በማቅረብ አካባቢን በማየት ከሚታወቀው ነገር በመነሳት ግልጽና አሳታፊ በሆነ አቀራረብ ጥልቅ ምሥጢራትን በመግለጽና በማሳየት እየቀረበ ያለ ሥልጠና ነው። ሁሉም ሠልጣኝ በመመልስ ፣በመጠየቅና በንቃት በመከታተል ሥልጠናውን እየተሳተፈ ይገኛል። #የመጀመሪያው ቀን ሥልጠና የተጠናቀቀ ሲሆን ነገም እንደሚቀጥል የወጣው መርሐ ግብር ያመለክታል።

ለሁለት ቀን የሚቆይ ሥልጠና ተጀመረ!! Read More »

ብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጅ ሀገረ ስብከት ጳጳስ በልዩ ልዩ የሙያ ዘርፍ ተሰማርተው በአዲስ አበባ ከሚገኙ ኦርቶዶክሳውያን ምእመናን ጋር በሀገረ ስብከቱ በሚከናወኑ ዕቅዶች ዙሪያ ውይይት አደረጉ።

ብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጳጳስ በሀገረ ስብከቱ እየተከናወኑና ወደፊት ሊተገበሩ በታቀዱ ዕቅዶች ዙሪያ በአዲስአበባ ከተማ ከሚገኙ ኦርቶዶክሳውያን ጋር በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ የነገረ መለኮት መማሪያ ክፍል የጋራ ውይይትና ምክክር አደረጉ። ለምክክሩ መነሻ የሚሆን ሰነድ የቀረበ ሲሆን በሰነዱ በሀገረ ስብከቱ ታሪካዊ ጉዞ፣ አሁናዊ ሀገረ ስብከቱ ያለበት ነባራዊ እውነታና ተግዳሮት፣ ወደፊት በሀገረ ስብከቱና በምእመናን መሥራት ያለበትን ተግባራት፣ የተሳታፊዎች ድርሻና አስተዋጽኦ ዙሪያ ሰፋ ያለ ሰነድ በፓወር ፖይንት ቀርቧል። ብፁዕነታቸው እስካሁን የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ማዕከል ከተማ ተኮር በመሆኑ የተነሳ በገጠር ያለው ብዙ ቁጥር ያለው ምእመናን ካህን፣ መምህርና ሰባኬ ወንጌል ባለመኖሩ በትምህርት እና ጠባቂ በማጣት ወደ ተለያዩ ቤተ እምነት እንዲሄዱ ምክንያት የሆነና ሂደቱም እየቀጠለ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ከተመሠረተ ጥቂት ዓመታት ያስቆጠረ ሲሆን በተለይ በሀገረ ስብከት ደረጃ የ10 ዓመት ስልታዊ ዕቅድ ታቅዶ ወደ ተግባራዊ ሂደት መግባቱ አንዱ ማሳያ በመሆኑ ይህን ሀሳብ ለመላው ማህበረሰብ መድረስ እንዳለበት የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል። እንደ ሀገረ ስብከት የቀረበው ጥናቱ ችግሮቹን በሙሉ የለየ ከመሆኑ በተጨማሪ የመፍትሔ ሃሳብ የተቀመጠ በመሆኑ ወደ ሥራ መግባት ያስፈልጋል ብለዋል ። በአዲስአበባ የሚኖሩ የቅድስት ቤተክርስቲያን ልጆችም በቀረበው የውይይት ሰነድ መነሻነት ሃሳብ የሰጡ ሲሆን በቀጣይ የሚጠበቅባቸውን ለመወጣት በሃሳብ ፣በገንዘብ ፣በእውቀት እንዲሁም ሌሎችንም በማስተባበር ጭምር እገዛ ለማድረግ ቃል ገብተዋል። ይህ መድረክ ቀጣይነት ያለው ሲሆን ሁሉም ኦርቶዶክሳውያን በገንዘባቸው በእውቀታቸው በሙያቸው ሀገረ ስብከቱን እንዲደግፉ ጥሪ የቀረበ ሲሆን በመጨረሻም በጉባኤው ማጠቃለያ ሶስት አባላት ያሉት አስተባባሪ ኮሚቴ በማቋቋም በብፁዕነታቸው ጸሎትና ቡራኬ ተጠናቋል።

ብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጅ ሀገረ ስብከት ጳጳስ በልዩ ልዩ የሙያ ዘርፍ ተሰማርተው በአዲስ አበባ ከሚገኙ ኦርቶዶክሳውያን ምእመናን ጋር በሀገረ ስብከቱ በሚከናወኑ ዕቅዶች ዙሪያ ውይይት አደረጉ። Read More »

ከሐምሌ 22 እስከ ሐምሌ 28 ቀን 2016 ዓ/ም ድረስ በሁሉም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ገዳማት የሚፈጸመውን የምሕላ ጸሎት አስመልክቶ ከቋሚ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

ከሐምሌ 22 እስከ ሐምሌ 28 ቀን 2016 ዓ/ም ድረስ በሁሉም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ገዳማት የሚፈጸመውን የምሕላ ጸሎት አስመልክቶ ከቋሚ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ‹‹ተማሕለሉ ወሰአሉ ኃበ አቡክሙ ሰማያዊ እስመ አብ ይሁበክሙ ኵሎ ዘሰአልክሙ…አባታችሁ የምትለምኑትን ሁሉ ይሰጣችኋልና ወደ ሰማይ አባታችሁ ለምኑ፣ ምሕላንም አውጁ›› ኢዩኤል 1፤14 ቅዱስ ያሬድበሀገር አስተማማኝ ሰላም ሲጠፋ በጾም በጸሎት በመወሰን፣ምሕላን በማወጅ ልባዊ በሆነ ተማሕጽኖ ሁሉን ማድረግ ወደሚችለው አምላካችን አግዚአብሔር ምልጃን ማቅረብ የሚያስፈልግ መሆኑን ከሀገራችን ሊቃውንት መካከል የመጀመሪያ የሆነው ቅዱስ ያሬድ ከሰማያውያን ዐውደ ማህሌት ሰምቶ በቀሰመው ጣዕመ ዜማ አበክሮ ይነግረናል፡፡ በመሆኑም ውሎ ማደር፣ ወጥቶ መግባት በአንዳንድ የሀገራችን አካባቢዎች ስጋት ከሆነ ሰነባብቷልና በእውነት የሚለምኑትን ሁሉ የሚሰማ እግዚአብሔር መተላለፋችንን ይቅር እንዲለን፣ ለሀገራችን ዘላቂ ሰላም፣ ለቤተ ክርስቲያናችን ፍቅር አንድነት፣ ለሕዝባችን ደኅንነት እንዲሰጥልን ከአንድነት ገዳማት ኅብረት በቀረበው ጥያቄ መነሻነት ምሕላ ማወጅ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ በሁሉም የሀገራችን ክፍልና በሌሎችም አህጉራተ ዓለም የምትገኙ መነኰሳትና መነኰሳይያት ከሐምሌ 22 እስከ ሐምሌ 28 ቀን 2016 ዓ.ም. ድረስ ለሰባት ተከታታይ ቀናት በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ሃይማኖታዊና ቀኖናዊ ትውፊት መሠረት የገዳማት ኅብረቱን ጥሪ ተቀብላችሁ የምሕላ ጸሎት እንድታደርሱ፣ በጤና ችግር ምክንያት ካልሆነ በስተቀር እስከ ዕርበተ ፀሐይ በመጾም ሱባኤ እንድትይዙ፣ ቋሚ ሲኖዶስ በኅብረተ መንፈስ ቅዱስ ከአደራ ጋር ያሳስባል፡፡ ሁሉም የቤተክርስቲያናችን አገልጋዮችና ምእመናን ሀገራዊ ሰላምን፣ መረጋጋትንና ፍቅር አንድነትን ለማስፈን ጾምና ጸሎት በታወጀበት የምሕላ ሳምንት ለገዳማውያኑ ፀጥታ ሲባል ወደ ገዳማት የምታደርጉትን ጉዞ ለጊዜው እንዲቆይ አድርጋችሁ መደበኛ ሥራችሁን በያላችሁበት ቦታ እየሠራችሁ እግዚአብሔር የገዳማውያኑን ጸሎት ሰምቶ ለሀገራችንና ለሕዝባችን ምሕረትን እንዲሰጥ በኅሊና ዝግጅት፣ በሐሳብ አንድነት ሆናችሁ በጾም በጸሎት እንድተጉ ቋሚ ሲኖዶስ መንፈሳዊ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡ ‹‹እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ››ሐምሌ 5 ቀን 2016 ዓ.ም.አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

ከሐምሌ 22 እስከ ሐምሌ 28 ቀን 2016 ዓ/ም ድረስ በሁሉም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ገዳማት የሚፈጸመውን የምሕላ ጸሎት አስመልክቶ ከቋሚ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ Read More »

“ተደራሽነት ያለው የሕዝብ ግንኙነት ለኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን” በሚል ርዕስ ለአህጉረ ስብከት የሕዝብ ግንኙነት ዋና ክፍል ኃላፊዎች ሲሰጥ የነበረው ሥልጠና ተጠናቀቀ።

“ተደራሽነት ያለው የሕዝብ ግንኙነት ለኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን” በሚል ርዕስ ለአህጉረ ስብከት የሕዝብ ግንኙነት ዋና ክፍል ኃላፊዎች ሲሰጥ የነበረው ሥልጠና ተጠናቀቀ። ግንቦት ፲፯ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም****አዲስአበባ -ኢትዮጵያ============= የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ “ተደራሽነት ያለው የሕዝብ ግንኙነት ለኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን” በሚል ርዕስ ለአህጉረ ስብከት የሕዝብ ግንኙነት ዋና ክፍል ኃላፊዎች በሕዝብ ግንኙነት ምንነት፣ አሠራር፣ አደረጃጀትና በእርቶዶክሳዊ ማኅበራዊ ሚዲያዎች አጠቃቀም ዙሪያ ሲሰጥ የነበረው ሥልጨና ተጠናቀቀ። በዛሬው እለትም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባሕር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ለአሰልጣኞችና በስልጠናው ላይ ለተሳተፉ የአህጉረ ስብከት የሕዝብ ግንኙነት ዋና ክፍል ኃላፊዎች የተዘጋጀላቸውን የምስክር ወረቀት ከቅዱስነታቸው እጅ ተቀብለዋል።በዚሁ ጊዜም ቅዱስ ፓትርያርኩ አባታዊ መልዕክት፣ ቃለ በረከትና ቃለ ምዕዳን አስተላልፈዋል። በዚሁ ጊዜም የተዘጋጀው በለ ፲ ነጥብ የአቋም መግለጫ ተነቧል። የአቋም መንለጫው ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል። ‹‹አምላከ ሰማይ ይረድአነ ወንህነ አግብርቲሁ ንትነሣእ ወነሐንጽ ሎቱ፡፡››‹‹የሰማይ አምላክ ያከናውንልናል፤ እኛም ባሪያዎቹ ተነሥተን እንሠራለን፡፡››ነህምያ 2፡20 ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፤ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፤ የባሕር ዳርና የሰሜን ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፤ ሊቀ ስዩማን እስክንድር ገብረክርስቶስ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ዋና ኃላፊ፤ ክቡራን የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የየመምሪያና ድርጅቶች ኃላፊዎች፤ ክቡራን ሠልጣኞች፡፡ ከሁሉ አስቀድሞ እግዚአብሔር ረድቶን የብፁዕ ወቅዱስ አባታችን እና የብፁዓን አባቶቻችን ጸሎት አግዞን ይህንን የቤተ ክርስቲያናችንን የሕዝብ ግንኙነት ሥራ ከፍ ወዳለ ደረጃ ማድረስ የምንችልበትን የሥልጠና፣ የውይይትና የምክክር መርሐ-ግብራችንን አጠናቀን በብፁዕ ወቅዱስ አባታችን ለመባረክ በመብቃታችን ታላቅ መንፈሳዊ ሐሴት የተሰማን መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን ያለችበትን ነባራዊ ሁኔታ በአግባቡ በመረዳትና ያሉባትን ፈተናዎች በጠንካራ የሕዝብ ግንኙነት ሥራ ለመወጣት በማሰብ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ለእኛ በየአህጉረ ስብከቱ ላለን የሀገረ ስብከት ሕዝብ ግንኙነት ክፍል ኃላፊዎች ካዘጋጀውና ከ ግንቦት 15 – 17 ቀናት 2016 ዓ/ም ከተሰጠው የሥልጠና፣ የውይይትና የምክክር መርሐ-ግብር ዘርፈ ብዙ እውቀትን ገብይተናል፡፡ በሥልጠና መርሐ-ግብሩ ያገኘነውን ዕውቀት፣ ግንዛቤና ምክረ-ሐሳብ መነሻ በማድረግም እግዚአብሔር አምላካችን እንደሚረዳን በማመንና የብፁዕ ወቅዱስ አባታችን እና የብፁዓን አባቶቻችንን ጸሎት ተስፋ በማድረግ በሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ቤተ ክርስቲያን የምትፈልግብንንና ዘመኑን የዋጀ መንፈሳዊ ሥራ ለመሥራት መዘጋጀታችንን ስንገልጽ በታላቅ ደስታ ነው፡፡ ለሦስት ቀናት በቆየው የሥልጠና መርሐ-ግብር፡-1.ኛ ቤተ ክርስቲያናችን ለሀገራችን ያበረከተቻቸውን ወደር የለሽ አስተዋጽኦዎች ተረድተናል፡፡2.ኛ ስለ ሕዝብ ግንኙነት ምንነት፣ ተልእኮ፣ የአፈጻጸም ስልትና የውጤታማነት ግምገማ ተምረናል።3.ኛ ስለ ሕዝብ ግንኙነት ሙያዊ ስነ ምግባር እና የሕግ ተጠያቂነት ከፍተኛ ግንዛቤ አግኝተናል።4.ኛ የቤተ ክርስቲያናችንን ልማትና ተግዳሮት በንቃት በመከታተል፤ የሚነሡትን አሉታዊ አመለካከቶች ወይም የተሳሳቱ ግንዛቤዎች በማጥራት በምእመናን እና በማኅበረሰቡ መካከል መተማመንና መከባበር እንዲኖር በትጋት መሥራት እንዳለብን ተረድተናል።5.ኛ ከጠባቂነት በመውጣት በቆራጥነት፤ በበቂ ክህሎት ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ወደ ፊት ለማሻገር ጠንክረን መሥራት እንዳለብን ተገንዝበናል፡፡ከእነዚህ ግንዛቤዎች በመነሣትም ቤተ ክርስቲያናችን በሕዝብ ግንኙነት መስክ ውጤታማ ትሆን ዘንድ የሚከተሉትን ጠቃሚ ተግባራት ለመፈጸም እኛ በሥልጠናው የተሳተፍን የአህጉረ ስብከት የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ኃላፊዎች እግዚአብሔር አምላካችንን አጋዥ አድርገን በብፁዕ ወቅዱስ አባታችንና በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ፊት ቃል እንገባለን፡፡6.ኛ የሕዝብ ግንኙነት ክፍሉን ከሀገረ ስብከት እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ድረስ በእቅድ በመምራት፣ ፈንድ በማፈላለግ፣ የሚዲያ ሠራዊትን በስልጠና በማጠናከርና የሚያስፈልጉ ግብአቶችን በማሟላት ውጤታማነቱን ለማረጋገጥ ቃል እንገባለን፡፡7.ኛ በአህጉረ ስብከት የሚከሰቱ ማናቸውንም አወንታዊ ዜናዎችና አሉታዊ ተግዳሮቶች ሳምንታዊ በሆነ መርሐ-ግብር ለመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ በተከፈተልን የግንኙነት መስመር ለማስተላለፍ ቃል እንገባለን፡፡8.ኛ የቤተ ክርስቲያናችንን ነባራዊ ሁኔታ በንቃት በመከታተልና ትክክለኛ መረጃዎችን በመስጠት፤ አሉታዊ አመለካከቶችን እና የተሳሳቱ ግንዛቤዎች የማጥራት ሥራን በትጋት ለመሥራት ቃል እንገባለን።9.ኛ ቤተ ክርስቲያናችን መሠረታዊ እሴቶቿን እንደ ጠበቀች፤ ከወቅታዊ ጉዳዮችና የመገናኛ መንገዶች ጋር በመላመድ በምታደርገው ጉዞ የሚገጥሟትን እንቅፋቶች በድል መሻገር እንድትችል የሚጠበቅብንን ሁሉ ለማድረግ ቃል እንገባለን፡፡10.ኛ ማኅበራዊ ሚዲያ የሌለን አህጉረ ስብከት የማኅበራዊ ሚዲያ ገጽ ከፍተን የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ሥርዓቷን፣ ዶግማዋን፣ ቀኖናዋን፣ ክብረ በዓላቶቿን፣ የአደባባይ በዓላቶቿን፣ የሀገረ ስብከታችንን የልማት፣ የስብከተ ወንጌልና አጠቃላይ እንቅስቃሴዎች ለምእመናንና ለቤተክርስቲያናችን ወዳጆች ተደራሽ ለማድረግ ቃል እንገባለን፡፡ለዚህም የቅዱስ አባታችንና የብፁዓን አባቶቻችን ጸሎት ትርዳን፡፡ ግንቦት 17 ቀን 2016 ዓ/ም.መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነትአዲስ አበባ – ኢትዮጵያ

“ተደራሽነት ያለው የሕዝብ ግንኙነት ለኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን” በሚል ርዕስ ለአህጉረ ስብከት የሕዝብ ግንኙነት ዋና ክፍል ኃላፊዎች ሲሰጥ የነበረው ሥልጠና ተጠናቀቀ። Read More »

የኢኦቴቤ መገናኛ ብዙሃን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት የቀጥታ የሳተላይት ቴሌቪዥን ሥርጭት ለመጀመር ባከናወነው ተግባር ለተሳተፉ አካላት የምስጋና ፕሮግራም እያካሄደ ይገኛል።

የኢኦቴቤ መገናኛ ብዙሃን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት የቀጥታ የሳተላይት ቴሌቪዥን ሥርጭት ለመጀመር ባከናወነው ተግባር ለተሳተፉ አካላት የምስጋና ፕሮግራም እያካሄደ ይገኛል። በመርሐ ግብሩ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ የሰሜንና ምሥራቅ አፍሪካ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የድርጅቱ የበላይ ኃላፊ በችግር ሰዓት የቆመ ጣቢያ መሆኑን ጠቅሰው በጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ብፁዕ አቡነ አብርሃም ደብዳቤ መነሻነት ለተራዱ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እና ሌሎች አካላት ምስጋና አቅርበዋል። ቀሲስ መዝገቡ ካሳ (ዶ/ር) የኢኦቴቤ ቴሌቪዥን ሥራ አስኪያጅ በእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግራቸው “ድርጅታችን የምሥረታ ጊዜውን አጠናቆ ተቋማዊ ቅርጽ ይዟል። በሀገር ውስጥና ውጭ ካሉ ምእመናን ከ160 ሺህ ዶላር በላይ በመሰብሰብ የቀጥታ ሥርጭት መሳሪያ ገዝተው ግዴታቸውን ተወጥተዋል። በዚህም በመንፈሳዊ ልጆቻችን ኮርተናል”ብለዋል። ለመሰረታዊ ለውጥ ጥናት እየተደረገ ነው ያሉት ሥራ አስኪያጁ ድርጅቱ የራሱን ሕንጻ መገንባት፣ የቋንቋ ተደራሽነት ማስፋት፣ የቴክኖሎጂ አቅምን ማሳደግና በጠንካራ ይዘት መስራት ትኩረት እንደሚሰጧቸው ገልጸዋል።

የኢኦቴቤ መገናኛ ብዙሃን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት የቀጥታ የሳተላይት ቴሌቪዥን ሥርጭት ለመጀመር ባከናወነው ተግባር ለተሳተፉ አካላት የምስጋና ፕሮግራም እያካሄደ ይገኛል። Read More »

Scroll to Top