በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት

Public Relation

“የሚመለከታቸው አካላት የዜጎችን ደኅንነት እንዲያስጠብቁ እና ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ሊሠሩ እንደሚገባ በአጽንዖት እናሳስባለን”ብፁዕ አቡነ ገሪማ ጳጳስ

ብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል በኦሮሚያ ክልል በአርሲ ዞን በደረሰው ጥቃት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገለጹ። የብፁዕነታቸው ሙሉ መልእክት እንደሚከተለው ነው። “በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ ነገር ግን አይዟችሁ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ”ዮሐ 16፥33 በኦሮሚያ ክልል በአርሲ ዞን በሚገኙ ኦርቶዶክሳውያን ላይ በደረሰው አሳዛኝ ጥቃት ሕይወታቸውን ባጡ እና በተጎዱ ወገኖቻችን ከልባችን አዝነናል። በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች በተደጋገመው በዚህ ድርጊት ቤተ ክርስቲያናችንን ከልብ የሚያሳዝን እና የሀገራችንን ዘላቂ ሰላም ጥያቄ ውስጥ የሚከት በመሆኑ የሚመለከታቸው አካላት የዜጎችን ደኅንነት እንዲያስጠብቁ እና ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ሊሰሩ እንደሚገባ በአጽንዖት ለማሳሰብ እንወዳለን።መአቱን በምሕረቱ ቁጣውን በትግዕስቱ ይመልስልን ዘንድ ሁልጊዜም ምላሽ ወደሚሰጠን አምላክ በጸሎት መጠየቅ ይገባናል። የልጆቻችንን ነፍስ ከቅዱሳን ማኅበር እንዲደምርልን፣ ያዘኑ የተከዙ ወገኖቻችንን ከሀዘናቸው እንዲያጽናናልን ጸሎታችን ነው። እግዚአብሔር ሀገራችንን ይባርክ!አባ ገሪማየጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጳጳስየቅዱስ ሲኖዶስ አባል

“የሚመለከታቸው አካላት የዜጎችን ደኅንነት እንዲያስጠብቁ እና ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ሊሠሩ እንደሚገባ በአጽንዖት እናሳስባለን”ብፁዕ አቡነ ገሪማ ጳጳስ Read More »

“ወኀረዩ እስጢፋኖስሀ ብእሴ ዘምሉእ ሃይማኖተ ወመንፈሰ ቅዱሰ – በእምነትና በመንፈስቅዱስ የተሞላውን እስጢፋኖስን መረጡ” ሐዋ 6፥5

እስጢፋኖስ ማለት አክሊል (ዘውድ)ማለት ነው።በአንደኛው መቶ ክፍለ ዘመን በሀገረ እስራኤል ተወልዷል።አባቱ ስምዖን እናቱ ሐና ይባላሉ። መጀመሪያ ከመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ በኋላም ከቅዱሳን ሐዋርያት ተምሯል። የመልካም ዛፍ መልካም ፍሬ ለመሆን የበቃ መንፈሳዊ ወጣት ነበር። ማቴ7፥17 በምእመናን ዘንድ መታመንንና መወደድን ያተረፈ፣ በወጣትነት ጊዜው በመንፈሳዊ ዕውቀትና በመንፈሳዊ ጥበብ ያደገ ፣በሃይማኖት የጸና፣መንፈስ ቅዱስ ያደረበት ሰው ነበር። በአንደኛው መቶ ከፍለ ዘመን ማለትም ከ34-41 ዓ/ም ባለው ጊዜ አይሁድና አሕዛብ ክርስትናን ከተቀበሉ በኋላ በመካከላቸው መነቃቀፍ ፣መተማማትና አለመግባባት ተፈጥሮ ጉዳዩ ከሐዋርያት ሲደርስ “ኢይደልወነ ከመንኅድግ ቃለ እግዚአብሔር ወንፀመድ ማዕዳተ – የእግዚአብሔርን ቃል ትተን ማዕድን እናገለግል ዘንድ አይገባንም” ሐዋ 6፥2 ብለው ችግሩን የሚፈቱ፣ በመልካምነታቸው የታወቁ፣ መንፈስቅዱስ የሞላባቸው፣ ጥበበኞች የሆኑ ሰባት ሰዎች እንዲመረጡ በማዘዛቸው ችግሩን እንዲፈቱ በሕዝቡ ተመርጠው በሐዋርያት ከተሾሙት 7 ዲያቆናት አንዱና ዋናው ነበር። በመሆኑም ሊቀ ዲያቆናት (የዲያቆናት አለቃ) ይባላል። የሐሥ 6፥6 ይሄ ምን ይነግረናል? ሐዋርያት መርጠው እንሹባችሁ አላሉም ።ሕዝቡን ራሳችሁ ምረጡ አሏቸው እንጂ። ይህ ነገርም ሕዝቡን ደስ አሰኝቷል። የአመራረጡ መስፈርት መልካምነት፣ ጸጋ መንፈስ ቅዱስና ጥበብ እንጂ ዝምድና አልነበረም ቀረቤታ አልነበረም ብሔር አልነበረም ቋንቋም አልነበረም እጅ መንሻሞ አልነበረም ጆሮ ጠቢነትም አልነበረም አማላጅም አልነበረም ጮሌነትም አልነበረም። በዚህ ሁሉ የመጣ(የተሾመ)ችግር ከማባባስ ባለፈ ችግር ፈቺ መሆን አይችልም ሰው ያለ ቦታው ተቀምጦ እንዴት ችግር ሊፈታ ይችላል? ለመንፈሳዊ ሹመት መንፈሳዊ ሰው ነው የሚገባው የዛሬዋ ቤተክርስቲያን ከዚህ ምን መማር አለባት ? በሊቀ ዲያቆንነቱ ጊዜ 8000 ማኅበረ ክርስቲያንን መርቷል። በአገልግሎቱ ኦሪት እጠፋ እጠፋ ፣ወንጌል እሰፋ እሰፋ ብላለች። በእኛ የአገልግሎት ጊዜ ክርስቲያንነት እሰፋ እሰፋ፣ ኢክርስቲያንነት እጠፋ እጠፋ ብሎ ይሆን?? በእስጢፋኖስ የአገልግሎት ጊዜ ናዖስ የሚባል መሠርይ (ጠንቅዋይ) (ጠንቋይ) በምትሐታዊ ተአምራት ሕዝቡን ሲያስት እውነተኛ ተአምራትን በማድረግ የናዖስን የምትሐት ሐሰትነትና ከንቱነት ለሕዝብ በማሳየት በእምነቱ እንዲጸና፣በምትሐታዊ ተአምር ከመታለል ራሱን እንዲጠብቅ በማስተማር የዕቅበተ እምነት ተልእኮውን በሚገባ ተወጥቷል። መሠርዩ ናዖስ በምስሐበ አጋንንትወደሰማይ ዐርጋለሁ ሲል በስመ እግዚአብሔር አውርዶ መሬት ላይ የጣለገባሬ ተአምራትም ነው ይባላል።የሐሥ6፥8የሄኖክን የትውልድ ሱባኤ፣የዳንኤልን የሰንበት ሱባኤየኤርምያስን የዕለት ሰባኤ አውጥቶኦሪትን ከወንጌል፣ዘመኑን ከዘመን ፣ትንቢቱን ከመድኅን አስማምቶ ዘመነ ሥጋዌ እንደደረሰ፣እግዚአብሔር ወልድ ሥጋ እንደለበሰ ሲያስተምር”ወሰእኑ ተቃውሞቶ”እንዲል እስጢፋኖስ የሚናገርበትን ጥበብ መቃወም ቢሳናቸው ተበሳጭተው ወደ ዐደባባይ አውጥተው በደንጊያ ወግረው ገድለውታል።እርሱም ሰማዕትነትን ተቀብሏል።ቀዳሜ ሰማዕት ይባላል።የሐዲስ ኪዳን ሰማዕታት መጀመሪያ ማለት ነው።”በእስጢፋኖስ አዕባን እመየኀልቁ፣ወገረኒ ኢያሱ በወርቁ”እንዳለ ባለቅኔው።ኦሪትን በሥርዓተ መላእክት ተቀብያለሁ ብሎ የሚመጻደው፣ነገር ግን ኦሪት የማይጠብቀው የአይሁድ ጉባኤ”ኦሪት ከወንጌል፣ዘመን ከዘመን፣ትንቢቱ ከመድኅን”እንደማይገጥም ለማሳየት ሲሉዓመተ አበውን ለመቀነስ፣ኦሪተ ሌዋውያንን ወደ ኦሪተ አይሁድ ብጡል ለመለወጥ ተገዷል ። “ከሸንጎ ቢረታ ሚስቱን ከቤት መታ” እንደሚባለው ማለት ነው።”እሙንቱሰ እምከንቱ ውስተ ከንቱ”እንዲል አካሔዱም ከጥፋት ወደፋት ሆኖበታል። እስጢፋኖስን እንጂ የእስጢፋኖስን እምነት መግደል አልቻለም “ዛሬም ክርስታያኑን እንጂ ክርስትናን መግደል አይቻልም።ማጥፋት አይቻልም ።መከራ ሊኖር ይችላል።ስደት ሊኖር ይችላል ፣ጫና ሊኖር ይችላል ነገር ግን ክርስቲያንነት ድል ያደርጋል እንጂ ድል አይሆንም።አይሸነፍም። ቅዱስ እስጢፋኖስ ግን “እግዚኦ ስረይ ሎሙ ዘንተ ኀጢአቶሙ ወኢትረሲ ቦሙ ጌጋየ” አቤቱ ይሄን በደል አታድርግባቸው” የሐሥ7፥60 በማለት ከክርስቶስ የተማረውን ይቅር ባይነትን ሉቃ 23፥34 ገዳዮቹን ይቅር በማለትና “ኦ እግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ ተመጠዋ ለነፍስየ” ጌታየ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ነፍሴን ተቀበል” የሐሥ 7፥59ከርስቶስን መስሎታል ሉቃ23፥46 1ኛ ቆሮ 11፥1“በዚያን ጊዜም በቤተክርስቲያን ላይ ታላቅ ስደት ሆነ” የሐሥ 8፥1 ማኅበረ እስጢፋኖስ ወደ እስያ ወቢታንያ ወደ ቀጰዶቅያ ተበትኗል።ይህም ውስጡ ጥበበእግዚአቦሔር ነበር በኢየሩሳሌም በኖሩ ሃይማኖት ይጸናል እንጂ አይሰፋም ነበር አሁን ግን ወንጌልንበደረሱበት ሥፍራ ሁሉ ስለሰብኩ የሃይማኖት መጽናት ብቻ ሳይሆን መስፋትም ሆነ። “እግዚአብሔርን ለሚወዱት እንደ ዐሳቡም ለተጠሩት ነገር ሁሉ ለበጎ እንዲደረግ እናውቃለን” ሮሜ 8፥28 ጥቅምት 17 ሢመቱ ጥር 1 ዕረፍቱ የሰማዕቱ ረድኤትና በረከት አይለየን። ሊቀ ማእምራን ሰሎሞን ፈጠነ

“ወኀረዩ እስጢፋኖስሀ ብእሴ ዘምሉእ ሃይማኖተ ወመንፈሰ ቅዱሰ – በእምነትና በመንፈስቅዱስ የተሞላውን እስጢፋኖስን መረጡ” ሐዋ 6፥5 Read More »

‎”በመልካም የተመሰከረላቸውን መንፈስ ቅዱስና ጥበብም የሞላባቸውን ሰባት ሰዎች ከእናንተ ምረጡ” (ሐዋ 6:3)‎በዚህ የአባቶቻችን የሐዋርያት መመሪያ መሠረት ከተመረጡ አገልጋዮች መካከል አንዱ ሐዋርያው ቅዱስ ፊልጶስ ነው።

በመጋቤ ምሥጢር ጥበቡ አናጋው ‎ ሐዋርያው ቅዱስ ፊልጶስ እግዚአብሔር ልኮት ኢትዮጵያዊውን ጃንረባ ባኮስን ያጠመቀው ነው።‎‎የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ታረክ፣ ምስረታ እና ልደት የሚያወሳ የታሪክም ሆነ የቤተክርስቲያን ምሁር ሐዋርያው ቅዱስ ፊልጶስን እና ቅዱስ ባኮስን ሳያነሳ ማለፍ አይቻለውም፡፡‎‎ምክንያቱም በኢትዮጵያ የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል እንዲሰበክ መነሻ የሆኑ ለእኛ ለኢትዮጵያውያን የወንጌል አባታቶቻችን ስለሆኑ ነው፡፡‎‎ከሰባቱ ሊቃነ-ዲያቆናት አንዱ ሆኖ የተሾመው ቅዱስ ፊልጶስ ትውልዱ ኢሲዶር ከምትባል የቄሳሪያ የወደብ ከተማ ሲሆን በቅዱስ እስጢፋኖስ ሞት ምክንያት ደቀመዛሙርት ከኢየሩሳሌም እስከተበተኑ ድረስ በኢየሩሳሌም ከሐዋርያት እግር ስር ሆኖ ተምሯል፡፡‎‎ከመንፈስ ቅዱስ መገለጥ በኋላ ሐዋርያት በኢየሩሳሌም ባደረጉት የመጀመሪያ የስብከት አገልግሎት በርካታ ምዕመናን አምነው ተጠመቁ፤ የምዕመናኑ ቁጥር እጅግ በመጨመሩ እና የአገልግሎቱ ዘርፉም እየበዛ በመሄዱ አገልጋዮችን መጨመር አስፈላጊ መሆኑን ባመኑ ጊዜ ሐዋርያት ቀደም ሲል በአርድትነት ሲያገለገሉ ከነበሩት መካከል ሰባቱን ሊቃነ-ዲያቆናት ለመጋቢነት መረጡ፡፡‎‎ምዕመኑን በመጋቢነት እንዲያገለግሉ ከተመረጡት ሰባቱ ሊቀ-ዲያቆናት መካካል አንዱ ቅዱስ ፊልጶስ ሐዋርያ ዘሰማርያ ወኢትዮጵያ ነው፡፡‎‎በ35ዓ.ም. ቅዱስ እስጢፋኖስ በአይሁድ እጅ በሰማዕትነት ማለፉ ተከትሎ በኢየሩሳሌም የነበሩት ማኅበረ ምዕመናን ተበተኑ፤ ቅዱስ ፊልጶስም ጊቶን ወደ ምትባል የስሞን መሠርይ የትውልድ ስፍራ ወደሆነች የሰማርያ ከተማ ሄደ፡፡‎‎በዚያም ሐዋርያዊ አገልግሎቱን በማጠናከር በርካታ ምዕመናን በኢየሱስ ክርስቶስ አምላክነት አምነው እንዲጠመቁ አስችሏል፡፡ በተለይ በጥንቆላ ግብሩ የሚታወቀውን ሲሞን መሠርይን በማሳመን ማጥመቁን ቅዱስ መጽሐፍ ዘግቦለታል፡፡ ሐዋ 8፡13።‎‎በሰማርያ ሳለ የጌታም መልአክ ፊልጶስን ተነሥተህ በደቡብ በኩል ከኢየሩሳሌም ወደ ጋዛ በሚወርደው በምድረ በዳው መንገድ ሂድ አለው፡፡ እርሱም ተነሥቶ ሂደ፡፡ እነሆ የኢትዮጵያ ንግሥት የህንደኬ ባላሟል እና የሀብት ንብረቷ ሁሉ አዛዥ የሆነ አንድ ኢትዮጵያዊ ጃንደረባ አገኘ፡፡‎‎ይህም ሰው ሊሰግድ ወደ ኢየሩሳሌም መጥቶ ነበር፡፡ ሲመለስም በሠረገላ ተቀምጦ የነቢዩን የኢሳይያስን መጽሐፍ ያነብ ነበር፡፡ መንፈስም ፊልጶስን “ሂድ ወደዚህ ሠረገላ ቅረብ” አለው፡፡ ፊልጶስም ፈጥኖ ወደ ሠረገላው ሂደ፤ ጃንደረባውም የነቢዩን የኢሳይያስን መጽሐፍ ሲያነብ ሰምቶ “ለመሆኑ የምታነበውን ታስተውለዋለህን?” አለው፡፡ ጃንደረባውም “የሚያስረዳኝ ሰው ሳይኖር እንዴት አድርጌ አስተውለዋለሁ” አለው፤ ቅዱስ ፊልጶስም ስለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል ሰበከለት፡፡ በመጓዝ ላይ ሳሉም ውሃ ካለበት ስፍራ ደረሱ ጃንደረባውም “እነሆ ውሃ እዚህ አለ ታዲያ እንዳልጠመቅ የሚከለክለኝ ምን ነገር አለ?” አለው፡፡ ፊልጶስም “በፍጹም ልብህ ካመንህ መጠመቅ ትችላለህ” አለው፡፡ ጃንደረባውም ‹‹ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ አምናለሁ›› ሲል መለሰለት፤ ሠረገላውም እንዲቆም አዘዘ፡፡‎‎ከዚያም ሁለቱም አብረው ወደ ውሃው ወረዱ፤ ፊልጶስም ጃንደረባውን አጠመቀው፡፡ ከውሃውም በወጡ ጊዜ የጌታ መንፈስ ፊልጶስን ነጥቆ ወደ አዛጦን ወሰደው። ሐዋ 8፣ 26-39። ወደ ቂሣርያ እስኪመጣ ድረስም በእየከተሞቹ ሁሉ እየተዘዋወረ ወንጌልን ሰብኳል፡፡ በቂሳርያ ሳለ ሚስት አግብቶ 4 ሴቶች ልጆችን ወለደ፤ እነርሱም ሀብተ ትንቢት የተሰጣቸው ደናግናል ነበሩ፡፡ ሐዋ 21፣8። በረጅም የወንጌል አገልግሎቱ ብዙ አይሁድን እና ሳምራዊያንን ወደ ክርስትና መልሶ ጥቅምት 14 ቀን በሰላም ማረፉን የታረክ መዛግብት ይናገራሉ፡፡‎‎የሐዋርያው የቅዱስ ፊሊጶስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን! መጋቤ ምሥጢር ጥበቡ አናጋው ጥቅምት 14/2018 ዓ.ም

‎”በመልካም የተመሰከረላቸውን መንፈስ ቅዱስና ጥበብም የሞላባቸውን ሰባት ሰዎች ከእናንተ ምረጡ” (ሐዋ 6:3)‎በዚህ የአባቶቻችን የሐዋርያት መመሪያ መሠረት ከተመረጡ አገልጋዮች መካከል አንዱ ሐዋርያው ቅዱስ ፊልጶስ ነው። Read More »

የሕግ ክፍልን በተመለከተ የግንዛቤ መስጫ መርሃግብር ተካሄደ!!

ኤክቱስ ጥቅምት 15/2018 ዓ.ም በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት የሕግ ክፍል ዐቢይ ኮሚቴ መቋቋሙን ተከትሎ ለተመረጡ ወረዳ ቤተ ክህነት ሠራተኞች፣ ለአድባራት አስተዳዳሪዎችና የሰበካ ጉባኤ አባላት የግንዛቤና የትውውቅ መርሃግብር የተካሄደ ሲሆን በመርሃግብሩ የሀገረ ስብከቱ የክፍል ኃላፊዎች ተሳትፈዋል። መርሃግብሩ በዘርፉ ባለሙያዎች ስለአስፈላጊነቱ እና ስለዝርዝር ጉዳዮች ገለጻ የተደረገ ሲሆን ሁሉም የኮሚቴው አባላት ራሳቸውን ለመርሃግብሩ ተሳታፊዎች አስተዋውቀዋል። በተጨማሪም ከተሳታፊዎች ሃሳብ፣ አስተያየት እና ጥያቄ የቀረበ ሲሆን ለተነሱ ጥያቄዎች የኮሚቴው አባላት ምላሽ ሰጥተዋል። በመጨረሻም የሀገረ ስብከቱ መንፈሳዊ ትምህርትና የካህናት አገልግሎት ክፍል ኃላፊ መልአከ ሰላም ቆሞስ አባ ዮሐንስ ምሕረቱ በጸሎት ፈጽመዋል።

የሕግ ክፍልን በተመለከተ የግንዛቤ መስጫ መርሃግብር ተካሄደ!! Read More »

ብፁዕ አቡነ ገሪማ ጳጳስ በክብር ዶክተር ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ እረፍት የተሰማቸውን ሀዘን ገለጹ!!

ኤክቱስ ጥቅምት 10/2018 ዓ.ም ብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል በቀድሞ የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝደንት በነበሩት የክብር ዶክተር በተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ከዚህ ዓለም ድካም በማረፋቸው ምክንያት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልጸዋል። ብፁዕነታቸው በመልእክታቸው እንደሀገረ እንደርሳቸው ያለ አስታራቂ፣ የዋህ እና ደግ አረጋዊ አባት ማጣታችን ምን ያህል አሳዛኝ እንደሆነ ገልጸዋል። በተጨማሪም ለመላው የእስልምና እምነት ተከዮች፣ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለመላው ኢትዮጵያውያን ወዳጆቻቸው መጽናናትን ይላክልን ብለዋል።

ብፁዕ አቡነ ገሪማ ጳጳስ በክብር ዶክተር ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ እረፍት የተሰማቸውን ሀዘን ገለጹ!! Read More »

ኢ-አማንያን የሥላሴን ልጅነት እንዲያገኙ እና የንስሐ አባት የሌላቸው ምዕመናን እንዲኖራቸው የማድረግ ሥራ ተጠናክሮ እየተሠራ እንደሚገኝ ተገለጸ!!

ኤክቱስ ጥቅምት 9/2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት በይርጋጨፌ ወረዳ ቤተ ክህነት ሥር የሚገኘው የይርጋጨፌ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አከባቢ ባሉ አዳሜና ኦሩ በተላ አከባቢ የሚኖሩ የንስሐ አባት የሌላቸው እና ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ጠፍተው የነበሩትን የመፈለግ ሥራ ተጠናክሮ እየተሠራ እንደሚገኝ መስከረም ሃያ ስድስት ቀን በነበረው ዘገባችን መዘገባችን ይታወሳል። በሁለቱ ቀበሌዎች ሁለት የስብከት ኬላዎች የተቋቋአ ሲሆን በዛሬው ዕለት የንስሐ አባት የሌላቸው እንዲኖራቸው በማድረግ በተሠራው ሥራ 8 አዳዲስ አማንያን ሥርዓተ ጥምቀት የተፈጸመላቸው ሲሆን በተመሳሳይ መልኩ አንዲት እኅት በቄደር ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ተመልሳለች። በአጠቃላይ ከዚህ በፊት ከተደረጉት መርሃግብራት ጋር 32 አዳዲስ አማንያን መገኘታቸው ተገልጿል። በተጨማሪም በካህናት እጦት ምክንያት 170 የንስሐ አባት የሌላቸው ምዕመናን እንዲኖራቸው፣ 44 የሰንበት ተማሪ ያልነበሩ ሕጻናትና ወጣቶች በሰንበት ትምህርት ቤት መዋቅር እንዲታቀፉ፣ እንዲሁም አንዲት የመቶ ሃያ ስምንት ዓመት ዕድሜ ያላቸው እናት ቅዱስ ሥጋውና ክቡር ደሙን እንዲቀበሉ የማድረግ ሥራ መሠራቱ ተገልጻል። በመርሃግብሩም የሀገረ ስብከቱ ዋና ጸሐፊ መልአከ ብርሃን አጥናፉ ማሞ፣ የሀገረ ስብከቱ ቁጥጥርና ምግባረ ሰናይ ክፍል ኃላፊ መምህር በየነ ክፍሌ፣ የወረዳ ቤተ ክህነቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ሰላም ይባቤ ይልማ፣ የደብሩ አስተዳዳሪ መጋቤ ኄራን ቀሲስ ጫንያለው፣ ሰባኪያነ ወንጌል፣ ዘማርያን እንዲሁም ካህናትና ምዕመናን ተገኝተዋል። ይህ የተጠናከረ ሥራ በሁሉም አጥብያ አብያተ ክርስቲያናት ላይ መሠራት እንዳለበት ተጠቁሟል። ፎቶ ልጅ ሀፒ

ኢ-አማንያን የሥላሴን ልጅነት እንዲያገኙ እና የንስሐ አባት የሌላቸው ምዕመናን እንዲኖራቸው የማድረግ ሥራ ተጠናክሮ እየተሠራ እንደሚገኝ ተገለጸ!! Read More »

እንኳን ደስ አላችሁ!የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ በከፍተኛ የሥራ አፈጻጸም ከምድብ ስድስት በአንደኛ ደረጃ ተሸላሚ ሆነ!!

ኤክቱስ ጥቅምት 08/2018 ዓ.ም በ44ተኛው ዓለም አቀፍ ጠቅላላ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት በከፍተኛ የሥራ አፈጻጸም ማለትም በመልካም አስተዳደር፣ ስብከተ ወንጌልን በማስፋፋት፣ ሰበካ ጉባኤን በማጠናከር፣ ሰንበት ትምህርት ቤትን በማደራጀት፣ ራስ አገዝ ልማትን በማስፋፋት፣ በገንዘብ ንብረትና አጠባበቅ፣ በቅርሳቅርስ ጥበቃ፣ ቅዱሳት መጻሕፍትንና የተለያዩ ኅትመቶችን በማሰራጨት፣ በምግባረ ሠናይ ሥራ ባሳየው ከፍተኛ አፈጻጸም በምድብ 6 ከተካተቱት አህጉረ ስብከቶች መካከል አንደኛ በመውጣት የምስክር ወረቀትና የመቶ ሃምሳ ሲሲ ባለ ሁለት እግር የሞተር ሳይክል ተሸላሚ ሆነ።

እንኳን ደስ አላችሁ!የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ በከፍተኛ የሥራ አፈጻጸም ከምድብ ስድስት በአንደኛ ደረጃ ተሸላሚ ሆነ!! Read More »

3372 አዳዲስ አማንያንን ማስጠመቁን የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ገለጸ!!

ኤክቱስ ጥቅምት 5/2018 ዓ.ም ከተጀመረ ሁለተኛ ቀኑን በያዘው ፵፬ተኛው ዓለም አቀፍ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ላይ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት በ2017 በጀት ዓመት ያሳካውን የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ተልእኮ ሪፖርት የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ሕይወት ብርሃኑ ክፍሌ አቅርበዋል። በሪፖርቱ እንደተገለጸው ሀገረ ስብከቱ በበጀት ዓመቱ ብፁዕ አቡነ ገሪማ የቤተ ክርስቲያንን ልጆች በማስተባበር የተዘጉ አብያተ ክርስቲያናትን እንዳስከፈቱ የተገለጸ ሲሆን በሁሉም ወረዳ ቤተ ክርስቲነት በመዘዋወር ሀዋርያዊ አገልግሎታቸውን መፈጸማቸውም ተገልጿል። የአብነት ትምህርት ቤትን በተመለከተ በአንዲዳ ለመጀመርያ ዙር የአብነት ተማሪዎች የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን በሟሟላት እና የቅዳሴ መምህር በመቅጠር ትምህርት እንዲሰጥ እንደተደረገ ተገልጿል። በተጨማሪም በሀገረ ስብከቱ ስብከተ ወንጌልን ለማስፋፋት ከ20 በላይ በተመረጡ አብያተ ክርስቲያናት ሕዝባዊ መንፈሳዊ ጉባኤያት የተደረገ ሲሆን በስድስቱም ወረዳ ቤተ ክህነቶች ካለፈው ዓመት በተሻለ መልኩ 3372 አዳዲስ አማንያን መጠመቃቸውን ገልጸዋል።

3372 አዳዲስ አማንያንን ማስጠመቁን የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ገለጸ!! Read More »

ብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሥር በሚገኘው የአረርቲ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን በደረሰው አደጋ የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገለጹ!!

“ይቤዙ እግዚአብሔር ነፍሰ አግብርቲሁ ወኢይኔስሑ ኩሎሙ እለ ይትዌከሉ ቦቱ – የባርያዎቹን ነፍስ እግዚአብሔር ይቤዣል በርሱም የሚያምኑ ሁሉ አይጸጸቱም”መዝ 33፥22 በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ምንጃር ሸንኮራ ወረዳ ሥር በሚገኘው አረርቲ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም በሕንጻ ግንባታ ምክንያት ለፊኒሽንግ ሥራ የተረበረበ እንጨት ተደርምሶ እስካሁን በሚያሳዝን ሁኔታ በውል ያልታወቁ ወገኖቻችን ሕይወታቸው ማለፉን ከሀገረ ስብከቱ ሚዲያ ስንሰማ እጅግ ከልባችን አዝነናል። ለሞቱት ወገኖቻችን እግዚአብሔር አምላካችን ሀገረ ሕይወትን መንግስተ ሰማያትን እንዲያወርስልን ከቅዱሳን ማኅበር እንዲደምርልን፤ ለቤተሰቦቻቸው መጽናናትን እንዲልክን ጸሎታችን ነው። እግዚአብሔር ሀገራችንን ይባርክ! አባ ገሪማየጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባልመስከረም 21/2018 ዓ.ም

ብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሥር በሚገኘው የአረርቲ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን በደረሰው አደጋ የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገለጹ!! Read More »

Scroll to Top