በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት

Uncategorized

ሀገረ ስብከቱ የሚስገነባው መንበረ ጵጵስና ተጎበኘ!!

ኤክቱስ ኅዳር 13/2018 ዓ.ም የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት አዲስ የሚያስገነባውን መንበረ ጵጵስና ብፁዕ አቡነ ገሪማ የሀገረ ስብከቱ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል፣ የሀገረ ስብከቱ የክፍል ኃላፊዎች፣ የማኅበረ ቅዱሳን ከፍተኛ አመራሮችና የዲላ ማዕከል ሥራ አስፈጻሚዎች ጎብኝተዋል። የማኅበረ ቅዱሳን የሥራ አስፈጻሚ የሆኑት መምህር ዋስይሁን በተመለከቱት ነገር ከመደሰታቸው በተጨማሪ “ሀገረ ስብከቱ ለብዙዎች አርአያ የሚሆን ነው” ያሉ ሲሆን በብፁዕነታቸው መደነቃቸውን ገልጸዋል።

ሀገረ ስብከቱ የሚስገነባው መንበረ ጵጵስና ተጎበኘ!! Read More »

የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ከማኅበረ ቅዱሳን ጋር ተወያየ!!

ኤክቱስ ኅዳር 13/2018 ዓ.ም የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ከማኅበረ ቅዱሳን ከፍተኛ አመራሮችና ከዲላ ማዕከል ሥራ አስፈጻሚዎች ጋር ውይይት አድርጓል። ውይይቱ ትኩረቱን ያደረገው ሀገረ ስብከቱ ከማኅበሩ ጋር በጋራ ለመሥራት በተፈራረመው ውል ላይ ሲሆን በቀጣይ ከማኅበሩ ጋር በጋራ ለመሥራት ባሰባቸው ሥራዎች ላይ ግልጽ ውይይት አድርጓል። በውይይቱ የሀገረ ስብከቱ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ብፁዕ አቡነ ገሪማ፣ የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ሕይወት ብርሃኑ ክፍሌ፣ የማኅበሩ ዋና ሥራ አስፈጻሚ መምህር ዋስይሁን፣ የማኅበሩ ደቡብ ማስተባበርያ ኃላፊ ቀሲስ አሰፋ ቦረና፣ የሀገረ ስብከቱ የክፍል ኃላፊዎች፣ የማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማዕከልና ዲላ ማዕከል ሥራ አስፈጻሚዎች ተሳትፈዋል።

የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ከማኅበረ ቅዱሳን ጋር ተወያየ!! Read More »

የአብነት ትምህርት ቤት ለመሥራት የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ!!

ኤክቱስ ኅዳር 13/2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማዕከል በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት በአንዲዳ መድኃኔዓለም ለሚያስገነባው የአዳሪ የአብነት ትምህርት ቤት በብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጸሎትና ቡራኬ የመሠረት ድንጋይ ተቀምጧል። ዝማሬ፣ ትምህርተ ወንጌልና በደቀመዛሙርት ቅኔ ቀርቧል። የአንዲዳ መድኃኔዓለም የአዳሪ የአብነት ትምህርት ቤት ሁለት የመጻሕፍት ደቀ መዛሙርት ቅኔ ቀርቧል። መምህር ዋስይሁን በላይ የማኅበረ ቅዱሳን ሥራ አስፈጻሚ ማኅበረ ቅዱሳን ቅዱስ ሲኖዶስ በሰጠው ኃላፊነት መሠረት የማኅበሩን አባላትና መላው ምዕመናንን በማስተባበር ገዳማት፣ አድባራትና የአብነት ትምህርት ቤቶች በሁለንተናዊ አገልግሎት ራሳቸውን እንዲችሉና ተተኪ ሊቃውንትን እንዲያፈሩ 1991 ዓ.ም ጀምሮ ከአንድ መቶ ሰባ በላይ የገቢ ማስገኛና የአገልግሎት መስጫ ፕሮጀክቶችን ሠርቶ ማስረከቡን ገልጸዋል። በተጨማሪም ማኅበሩ በ2018 ዓ.ም ለመተግበር ከያዘው ዕቅድ መካከል በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት የሚገኙ የቤተ ክርስቲያን ልጆችን በማስተባበር በአንዲዳ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን የአብነት ትምህርት ቤት ለመገንባት መዘጋጀቱንና ግንባታውም 14 ወራትን እንደሚቆይ ገልጸዋል። በተጨማሪም ማኅበሩ ከሀገረ ስብከቱ ጋር በጋራ መሥራት የሚስችለውን የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል። በሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ በመልአከ ሕይወት ብርሃኑ ክፍሌ ጋባዥነት ብፁዕ አቡነ ገሪማ የሀገረ ስብከቱ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ የሰጡ ሲሆን ማኅበረ ቅዱሳን እጅግ በጣም ብዙ ገዳማትን ከመበተን ከማዳኑ በተጨማሪ በርካታ የአብነት ትምህርት ቤቶችን ማጠናከር ቀዳሚ ተግባሩ መሆኑን ከመግለጻቸው በተጨማሪም ከማኅበሩ ጋር በርካታ ሥራዎችን በጋራ እንደሚሠሩ ገልጸዋል። በመጨረሻም ግንባታ ለመጀመር የታሰበበት ቦታ እንዲሁም ላለፈው አንድ ዓመት የአብነት ትምህርት ቤቱ መንፈሳዊ ትምህርት ሲሰጥበት የነበረው የተማሪዎች ማደርያ፣ ጽሕፈት ቤት፣ የመማርያና የመመገቢያ ክፍሎች በተጨማሪም ወደፊት የተለያዩ ልማቶችን ለመሥራት የታሰበበት ቦታ ጉብኝት ተደርጎ የመርሃግብሩ ፍጻሜ ሆኗል።

የአብነት ትምህርት ቤት ለመሥራት የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ!! Read More »

ሰጠቀ ባሕረ ወአኅለፎሙ (ባሕርን ከፍሎ አሻገራቸው።) መዝ ፸፷፥፲፫

ኅዳር ፲፪ በቅዱስ ሚካኤል ተራዳኢነት በሙሴ መሪነት እግዚአብሔር እስራኤልን ከግበፅ ባርነት ነጻ ማውጣቱን የምናከብርበት በዓል ነው ። ይኸውም ወጡ ለማለት ወረዱ ማለት ይቅድማልና በምን ምክንያት እንደወረዱ እንመልከት።እስራኤል ማለት ሕዝበ እግዚአብሔር ማለት ሲሆን ሥርዎ ሃይማኖት በመባል የሚታወቀው የአብርሃም የልጅ ልጅ ለያዕቆብ የተሰጠ ስም ነው ። ይህ ሕዝብ በታላቁ በአባቱ በአብርሃም በኩል ዘርህን እንደ ሰማይ ኮከብ አበዛዋለሁ የተስፋይቱንም ምድር አወርሰዋለሁ ተብሎ የተነገረለት እግዚአብሔርም የማዳን ሥራውን ለመስራት ያቀደበት ቢሆንም ቅሉ ዘፍ ፲፭ ፥፭-፲፪ በተቃራኒው ደግሞ ከዚሁ ምዕራፍ ሳንወጣ ዘፍ ፲፭ ፥፲፫ ላይ ስንመለከት“ዘርህ ለእርሱ ባልሆነች ምድር ስደተኞች እንዲሆኑ በእርግጥ እወቅ፤ ባሪያዎች አድርገውም አራት መቶ ዓመት ያስጨንቋቸዋል።ተብሎ ትዕቢት ተነግሮበት የነበረ ሕዝብ ነው። በጣም የሚገርመው ይህ ሕዝብ ታላቅ ሕዝብ እንደሚሆን የተስፋይቱን ምድር (ከነዓንን) እንደሚወርስ እግዚአብሔር ወልድም ከእርሱ ተወልዶ እንደሚያድነው ተስፋ ቢኖረውም በሌላ በኩል ደግሞ ለ፬፻ ዓመት በስደት ፣በባርነት ፣ በሰቆቃና በኀዘን እንደሚኖር ተነግሮበት ነበር። የእግዚአብሔር ቃል ይፈጸም ዘንድ ግድ ነውና ይህ ትንቢት በተነገረ በ፪፻ ወ ፲፭ ዓመት እስራኤል የተባለው ያዕቆብ እርሱና ቤተሰቦቹ ፸ ሆነው ወደግብፅ መሰደዳቸውን መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል። ለጊዜው በሀገራቸው የተከሰተውን የረሀብ ዘመን በወንድማቸው በዮሴፍ አማካኝነት በጥጋብ ቢያልፉትም በኋላ ግን በተለይም የወንድማቸው የዮሴፍን ሞት ተከትሎ የመጣባቸው መከራ ተዘርዝሮ የሚያልቅ አልነበረም። (በዘጸ ፩፥፰ በግብፅም ዮሴፍን ያላወቀ አዲስ ንጉሥ ተነሣ )ተበሎ እንደተጻፈው ይህ ንጉሥ የዮሴፍን ደግነት ፣ ጥበብ ፣ ክብር እና መጋቢነት ያላወቀ፣ ልቡ በክፋት የጸና፣ አንደበቱ በበቀል የተመላ፣ የሰይጣን ግብር አስፈጻሚ ነበር ማለት ብቻ ሳይሆን እርሱም ሥጋ የለበሰ ሰይጣን ነበር ቢባል ማጋነን አይሆንም ። ከዚህ ሰው ንግሥና በኋላ በእስራኤል ላይ ፅኑዕ የሆነ መከራ መጣባቸው ። በደስታቸው ላይ ኀዘን፣ በእረፍታቸው ላይ ስቃይ፣ በልተው በማደራቸው ፋንታ ረሀብ፣በክብራቸው ፋንታ ውርደት መጣባቸው በእስራኤላውያን መብዛት እረፍት ያጣው ፈርዖን ዘጸ፩፥፲ ስንመለከት (እንዳይበዙ፥ ሰልፍም በተነሳብን ጊዜ ጠላቶቻችንን አግዘው እንዳይወጉን ከምድሪቱም እንዳይወጡ፥ ኑ እንጠበብባቸው፡” አለ) ይለናል። ፈርዖን እስራኤላውያንን ለማጥፋት ጥበብን ይሻ ነበር እግዚአብሔር ያበዛውን ማጥፍት ባይቻልም ፈርዖን ግን ፍላጎቱን ለማሟላት የጥፋት ጥበብን ፈለገ። ሰው ከእግዚአብሔር ፈቃድ ሲወጣ ሀሳቡ የጥፋት፣ ጥበቡ የጥፋት፣ ግብሩ የጥፋት አመለካከቱ ሁሉ የጥፋት ይሆንበታል ። ፈርዖን ሀሳቡን እውን ለማደረግ በእስራኤላውያን ላይ በዙ ግፍ የፈጸመ ሲሆን የተወሰኑት፦ጡብ ማስጣልኖራ ማስወቀጥጭቃ ማስረገጥፈርዖን እስራኤላውያንን በእነዚህና በመሳሰሉት ስራዎች እያሰቃየ ፌቶም ፣ ራምሴና ዖን የሚባሉ ሦስት ከተሞችን በእነሱ ላብ ፣ ጉልበትና ደም አስገንብቷል ።ፈርዖን ከዕብራውያን ስዎች አንድም ሰው ለቅጽበት ስንኳ እረፍት ማግኘት እንደሌለበት ትእዛዝ ሰጥቷል ።ይህንም ያደረገው በሁለት ምክንያት ነው ፦ ፩ኛ በስራ ተጠምደው ከዋሉ የጦር ልምድ አይኖራቸውም ከጠላቶቻችንም ጋር ተባብረው አያጠፋንም ብሎ ነው ። ፪ኛ ወንዶች ጭቃ ሲረግጡ ሴቶችም ኖራ ሲወቅጡ ከዋሉ ወንዶችም ወደ ሴቶች ፣ ሴቶችም ወደ ወንዶች አይደርሱም በዚህ ምክንያት ዕብራውያን እንዳይወልዱና እንዳይበዙ ለማድረግ ነበር። እውነት ለመናገር በዕብራውያን ላይ የደረሰው ግፍ መጠን የሌለው ነው ፣ ምጥ የተያዘች እናት ስንኳ ያለእረፍት እያማጠች ጭቃ የረገጠችበት ዘመን ነው ። በዚያ ዘመን አንዲት ራሔል የምትባል ፣ውድ ባለቤቷ ሮቤልን በሞት ያጣችና መንታ የጸነሰች እናት ነበረች። በባለቤቷ ፋንታ ጭቃ እንደትረግጥ ተገደደች፣ በዚያን ሰዓት ምጥ መጣ ፣አምጣ ለመውለድ እኳን ፈቃድ ብትጠይቅ አልተፈቀደላትም ።እያማጠችም ጭቃ እየረገጠችም በነበረችበት ሰዓት ወለደች። ሆኖም ራሔል የነበረችው አልጋላይ ሳይሆን ጭቃ ላይ ስለሆነ መንተኞች ልጆቿ ከወደ ጭቃው ተቀላቀሉ ።የልጅ ፍቅር ያንገበገባት ራሔል ምጧን ረስታ ልጆቿን ለማንሳት ብትሞክሮም ከጭቃው ጋር አብራ እንድትረግጣቸው ተገደደች።የሰው ደም ግንብ ያጸናል ተብሎ ተነገረ ።ዛሬም በሀገራችን የሰው ደም ግንብ ያጸናል የተባለው የግብፅ አዋጅ የታወጀ ይመስላል ምን አልባት ፈርዖን ወደኢትዮጵያ መጥቶ ይሆን? እናም ራሔል እንባዋን ወደ ሰማይ ረጨች የራሔል እንባ የዕብራውያንን እንባ ቅድመ እግዚአብሔር አደረሰች እግዚአብሔርም ሰማቸው። ሙሴንም ከግብፅ እንዲያወጣቸው ላከላቸው ። ዕብራውያንን ነፃ ለማውጣት እግዚአብሔር ሙሴን አስነሳ።ከሚቀበሉት መከራ አንዱ የእስራኤላውያን ወንዶች ልጆች መገደል ነበር።በዘጸ ፩፣፲፮ እንደምናነበው ፎሀ እና ሲፓራ የተባሉ የግብፃውያን ሴቶች የዕብራውያንን ሴቶች አንዲያዋልዱ እና ወንድ ከተወለደ ደግሞ እንዲገድሉ ከፈርዖን ትእዛዝ ተሰጥቷቸው ነብር።በዚህ መሠረት ከእስራኤል ወንድ ልጅ ሲወለድ ይሞት ነበር ከዚህ የተረፈውም በባሕር ይጣል ነባር ። ሙሴን ግን እግዚአብሔር ጠበቀው።በንጉሡም ቤት ለ፵ ዓመት አኖረው ።እስራኤልን ይታደግ ዘንድ እግዚአብሔር መርጦታልና።በኋላም ጊዜው ሲደርስ እግዚአብሔር ሙሴን በ፹ ዓመቱ ወደግብፅ ላከው ።ሙሴ ከእግዚአብሔር የተሰጠውን ተአምር ለፈርዖን ካሳየ በኋል ሕዝቤን ልቀቅ ይልሀል እግዚአብሔር አለው ።ፈርዖንም እግዚአብሔርን አላውቅም ሕዝቤንም አለቅም በማለት ልቡን በክፋት አጸናው።በፈርዖን የልቡና ክፋት ምክንያት እግዚአብሔር በግብፃውያን ላይ ዘጠኝ መቅሰፍት አስረኛ ሞተ በኩርን አመጣባቸው።በተቃራኒው ዕብራውያንን ግን ከዚህ ሁሉ መቅሰፍት እየጠበቀ ያበዛቸው ነበር።የፈርዖን አመጽ ካመጣው መቅስፍት አንዱ የግብፅ ውሃዎች በሙሉ ደም መሆን ነበረ የግብፅ ሰዎችም ለሰባት ቀን የሚጠጡት ውሃ በማጣት አልቀዋል። በመጨረሻም ሞተ በኩር መጣ የግብፅ ምድርም ከሰው ጀምሮ እስከ እንስሳ ድረስ የበኩር የሆነውን (መጀመርያ የተወለደውን)በሞት አጣች ።ዘጸ ፲፪፣፲፪ ዕብራውያንን ግን ይህ ሁሉ እንዳያገኛቸው የአማናዊው በግ የክርስቶስ አምሳል የሆነውን የፋሲካውን በግ አርደው ስጋውን እንዲበሉ ደሙንም የቤታቸውን በር እንዲረጩት እግዚአብሔር ለሙሴ አዝዞት ስለነበር ሞተ በኩር ከበራቸው እደረሰ ተመልሷል።ከዚህ በኋላ የሚመራውን ሕዝብ በሞት ያጣ ፈርዖን ዕብራውያን የሶስት ቀን መንገድ ሄደው መስዋዕት ሰውተው እንዲመለሱ ፈቀደላቸው ።እስራኤላውያን ግን ለብዙ ዘመን የተገዙበትን ወርቅና ብር በተውሶ ምክንያት ይዘው ወጥተዋል ። ውስጡ ግን ጥበበ እግዚአብሔር ነበር ።ፈርዖን ከመከራው ጽናት የተነሳ በፈቃዱ ቢለቃቸውም ተከትሎ ማሳደዱን ግን አልተወም ነበር።እግዚአብሔርም ዕብራውያንን በሰባት ደመና እየመራ ጠበቃቸው፩ኛው ከላይ የፀሐይን ሙቀት ይከላከላል፪ኛው ከስር እንቅፋት እንዳያገኛቸው፫ኛው በቀኝ ጠላት እንዳይጎዳቸው፬ኛው በግራ ከሚመጣ ጠላት ይጠብቃል፭ኛው በኋላ ከሚመጣ፮ኛው በፊት ከሚመጣ፯ኛው የሶስት የአራት ቀን መንገድ ሲጠርግላቸው ውሎ ማታ ያበራላቸው ነበር። ፈርዖንም ተከትሏቸው ባሕረ ኤርትራ ሲደርሱ ድምጻቸውን እየሰማ ሳያገኛቸው የቀረው በደመና ስለተከበቡ ነው ።እስራኤልን በፊታቸው የኤርትራ ባሕር በኋላቸው የፈርዖን ሰራዊት ሲያስጨንቃቸው አደረ ።አይ ያች ሌሊት ምን አይነት ሌሊት ናት? እነሱ ተጨነቁ እንጅ እግዚአብሔር ግን በደመና እየጠበቃቸው ነበር።ጎህ ሲቀድ እግዚአብሔር ተአምሩን ገለጠ ሙሴን ባሕሩን በተአምረኛው በትሩ እንዲመታው አዘዘው ሙሴም የታዘዘውን አደረገ ።እግዚአብሔርም ባሕሩን ከፈለ ዕብራውያንንም በሰላም ባሕርን ከፍሎ አሻገራቸው።ፈርዖንም እንደ ዕብራውያን እሻገራለሁ መስሎት ከነሠራዊቱ ወደባሕር መግባቱ አልቀረም።እግዚአብሔር ሁሉም እስኪገቡ ጠበቃቸው ።ዕብራውያን ከባሕር ሲወጡ ግብፃውያን ወደባሕር ሲገቡ ሙሴ ለሁለተኛ ጊዜ ባሕሩን በብትሩ መታ ባሕሩም ወደቀደመ ማንነቱ ተመለሰ ።ፈርዖንም ከነሰራዊቱ ውሃ ሆኖ ቀረ። የዕብራውያንን ልጆች በውሃ ያስጣለው ፈርዖን ራሱም በውሃ ሰጠመ ።ዕብራውያን በሰላም ተሻግረው አምላካቸውን አመሰገኑ ክፋተኞች ግን በክፋታቸው ሰጠሙ ።የክፋዎች መጨረሻቸው ስጥመት ነው ።የመልካሞች ግን ባሕርን ከፍሎ መሻገር ነው።እግዚአብሔር ሆይ እኛንም ከኀጢአት ባሕር ያሻግረን ዘንድ ሙሴን ላክልን። መምህር መልአክ መሠለየአንዲዳ መድኃኔዓለም የአዳሪ የአብነት ትምህርት ቤትየትርጓሜ መምህር

ሰጠቀ ባሕረ ወአኅለፎሙ (ባሕርን ከፍሎ አሻገራቸው።) መዝ ፸፷፥፲፫ Read More »

የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጽሕፈት ቤት ለገደብ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የመጽሐፍ መምህር አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል!

የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጽሕፈት ቤት ለገደብ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የመጽሐፍ መምህር አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል! Read More »

“ተነሣ ሕፃኑንና እናቱን ውሰድ” (ማቴ 2:13፣ 19-20)

“ተነሣ ሕፃኑንና እናቱን ውሰድ” (ማቴ 2:13፣ 19-20) ሕዳር 6 የመልአኩን ቃል በመስማት ወደ ግብፅ የተሰደዱትን የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን፣ የልጇን የኢየሱስ ክርስቶስን፣ የአረጋዊ ዮሴፍን እና የሰሎሜን ጉዞ የምናስታውስበት ዕለት ነው። ንጉሥ ሄሮድስ የጌታችንን ሕይወት በፈለገ ጊዜ የጌታ መልአክ በሕልም ለዮሴፍ ታይቶ “ተነሥተህ ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ ወደ ግብፅ ሽሽ” (ማቴ 2፡13) አለው። እመቤታችንና ታዛዥና ታማኝ ቅዱስ ዮሴፍ ተነስተው በሌሊት ሄዱ፤ ለሦስት ዓመታት ያህልም እንግዳ ሆነው ኖረዋል። ጊዜው ሲፈጸም መልአኩ እንደገና ተገለጦ “የሕፃኑን ነፍስ የፈለጉት ሞተዋልና ተነሣ ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ ወደ እስራኤል ምድር ሂድ” (ማቴ 2፡19-20) የሚል መልእክት ነገረው። ከዓመታት ስደትና መከራ በኋላ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም፣ ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ፣ ዮሴፍ እና ሰሎሜን በደቡብ ግብፅ በሚገኘው የቁስቋም ተራራ ደረሱ። እግዚአብሔር ለሙሴ “የቆምክበት ስፍራ የተቀደሰ ምድር ነውና ጫማህን አውልቅ” (ዘጸአት 3፡5) ብሎ እንደተናገረው ክርስቶስ በዚያ ስላደረ ተራራው የተቀደሰ ቦታ ሆነ፤ የፍርሃት ቦታን ወደ በረከት ማደሪያ ለወጠው። እስራኤላውያንን በምድረ በዳ የመራቸው አምላክ ልጁን ወደ ግብፅ መራው፡፡ ይህም ማዳኑ ትውልድን እንደሚሸፍንና ፈተናዎችን ሁሉ ወደ መዳን መንገድ እንደሚቀይር አሳይቷል። የክርስቶስ መገኘት ምድርን ቀደሰ፣ በአንድ ወቅት በጨለማና በጣዖታት የተሞላ ቦታን አበራ በዚህም እሱን ለሚያምኑት ሁሉ ተስፋን ሰጥቷል። የእመቤታችንና የልጇ ጉዞ የነቢያትን ትንቢት ፈጽሟል። ኢሳይያስ፣ “እነሆ እግዚአብሔር በፈጣን ደመና ላይ ተቀምጦ ወደ ግብፅ ይመጣል፣ የግብፅም ጣዖታት በፊቱ ይንቀጠቀጣሉ” ኢሳይያስ 19፥1 በማለት ትንቢት ተናግሯል። ሆሴዕም “ልጄን ከግብፅ ጠራሁት” ሆሴዕ 11፥1፤ ማቴዎስ 2፥15 ብሏል። ሙሴ በአንድ ወቅት እስራኤላውያንን በእግዚአብሔር ቸርነት ከግብፅ ባርነት ወደ ነፃነት እንደመራቸው ኢየሱስ ክርስቶስም የሰው ልጆችን ከኃጢአት ባርነት ነፃ ለማውጣት ወደ ግብፅ ገባ። የመጀመርያው ስደት ሀገርን ነጻ አወጣ፤ ሁለተኛው ስደት ለሰው ልጆች ሁሉ ድኅነትን አቀረበ። ሁለቱም ጉዞዎች የእግዚአብሔርን ኃይል፣ ምሕረቱንና የማይለወጥ የማዳን እቅዱን ያሳያሉ። የቁስቋም ተራራ የቅድስናና የመሸሸጊያ ምልክት በመሆን ክርስቶስ የሚኖርበት ቦታ ሁሉ የተቀደሰ እንደሚሆንና ምእመናን በሚያምኑበት ቦታ ሁሉ “ሁለት ወይም ሦስት ሆነው በስሜ በሚሰበሰቡበት ስፍራ እኔ በመካከላቸው እገኛለሁ።” ማቴ 18:20 ባለው አምላካዊ ቃሉ በመካከላቸው እንደሚገኝ ያስታውሰናል። ዛሬ ብዙ ክርስቲያኖች ስለ ክርስቶስ ስም ስደት፣ መከራና ሞት ይደርስባቸዋል። ሆኖም ልጁን በግብፅ የጠበቀው አምላክ ሕዝቡን መጠበቁን ቀጥሏል። ፈተናዎች በኢየሱስ ክርስቶስ የሚያምኑትን አያሸንፉም፤ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም፣ ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ፣ ዮሴፍ እና ሰሎሜን እንደመራው፣ እያንዳንዱን አማኝ በሕይወት ፈተናዎች ውስጥ ይመራል፣ ፍርሃትን ወደ እምነት እና አደጋን ወደ መንፈሳዊ እድገት ይለውጣል። እግዚአብሔር ስደትን ወደ መመለስ፣ መከራን ወደ ቅድስና፣ ምድረ በዳንም ወደ አምልኮ ቦታ ይለውጣል። እኛም እንደ ቅዱስ ዮሴፍ በመታዘዝ እንነሳ፤ ቅዱስ ስሙን “ነፍሴ ጌታን ታከብረዋለች፣ መንፈሴም በአምላኬ በመድኃኒቴ ሐሴት ታደርጋለች” (ሉቃስ 1፥46-47) ብላ እመቤታችን እንዳመሰገነች እናክብረው። ፈተናዎች ቢከብቡንም እግዚአብሔር መጠጊያችን ነው። ክርስቶስ በሚኖርበት ቦታ ሁሉ ሰላም አለ፤ እናቱ በምትማልድበት ስፍራ ሁሉ ድል አለ። ምሕረቱን አጥብቀን እንያዝ፣ በመግቦቱ እንታመን፣ በማዳኑም ደስ ይበለን። እግዚአብሔር አምላካችን ከበዓሉ ረድኤት በረከት ያሳትፈን፤ ለሀገራችን ሰላምን፣ ለሕዝባችን ፍቅርን አንድነትን ያድለን፡፡ የእመቤታችን አማላጅነት አይለይን፡፡ አሜን፡፡ ኅዳር 6/2018 ዓ.ም ቀሲስ ጤናው እንዳላማውየጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከትየፕሮጀክት ማናጀር

“ተነሣ ሕፃኑንና እናቱን ውሰድ” (ማቴ 2:13፣ 19-20) Read More »

የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጽሕፈት ቤት ከዚህ በታች ባለው ክፍት የሥራ መደብ መስፈርቱን የሚያሟላ ሠራተኛ አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።

የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጽሕፈት ቤት ከዚህ በታች ባለው ክፍት የሥራ መደብ መስፈርቱን የሚያሟላ ሠራተኛ አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል። Read More »

ቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ

ቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ ‼️ቅዱስ ማርቆስ ሐዋርያና ወንጌላዊ እንዲሁም ሰማዕት ነው፡፡ ከዚህም ጋር የእስክንድርያ ቤተክርስቲያን መሥራች አባት ነው፡፡ ወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ ኢየሩሳሌም ውስጥ ክርስቲያኖች በቤቷ ለጸሎትና ለትምህርት ይሰበሰቡ የነበረችው የማርያም ልጅ ሲሆን አባቱ አርስጦሎስ አጎቱ በርናባስ ነበሩ፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት ሁል ጊዜ በእናቱ ቤት እየተሰበሰቡ ጸሎት በማድረግ ፈጣሪያቸውን ያመሰግኑ ነበር፡፡ « ማርቆስ በተባለ ዮሐንስ ቤት ሐዋርያት ይጸልዩ ነበር፡፡ »(የሐዋ 12፡12) እናቱ ማርያም እጅግ የከበረች ባለጸጋ እንደነበረችም በመጸሐፈ ስንክሳር ተገልጿል፡፡ቅዱስ ማርቆስ በትውልዱ ዕብራዊ ሲሆን ቤተሰቦቹ ግን ይኖሩ የነበሩት ሲረኒካ በተባለችውና በዛሬዋ ሊቢያ ምዕራባዊ ጠረፍ በተቆረቆረችው ከተማ ነበር። ነገር ግን የሰሜን አፍሪቃ ዘላን ጎሳዎች በየጊዜው በከተማው ጥቃት እየሰነዘሩ ቤተሰቦቹን አላስቀምጥ ስላሏቸው ወደ ትውልድ ሀገራችው ኢየሩሳሌም በመመለስ ቤት ሰርተው ተቀመጡ።ቅዱስ ማርቆስ በመጀመሪያ ስሙ ዮሐንስ እየተባለ ይጠራ ነበር እናቱም ልጇን ማርቆስን የዕብራይስጥና የዮናናውያን ቋንቋ አስተምራው ነበር ፡፡ ቅዱስ ማርቆስ በወጣትነት ዘመኑ የጌታን ትምህርት ሰምቶ ልቡ ስለተነካ ሁሉን ነገር ትቶ የክርስቶስን ወንጌለ መንግስት ሰማያት ለመስበክ ቆርጦ ተነሳ ጌታ ካረገ በኋላ ቅዱስ ማርቆስ ከቅዱስ ጴጥሮስ ጋር በመሆን ወንጌልን በማስተማሩ ቅዱስ ጴጥሮስ ልጄ እያለ ይጠራዋል፡፡(1ኛ ጴጥ 5፡12) ባሕረ ጥበባት ቅዱስ ያሬድ ስለዚህ ታላቅ ወንጌላዊ ተጋድሎ ሲመሰክር እንዲህ ብሏል ፡- « ወአንተሰ ትልወኒ በትምህርትየ ወበግዕዝከ ዘመሀርኩከ አስተፋጥን ትሬሲ ርእስከ ኅሩየ ለእግዚአበሔር ማርቆስ ክቡር ወንጌላዊ ዐቃቢሁ አንተ ለልዑል ድርገተ ኮንከ እንተ ላዕለ ኀይል ብእሴ እግዚአብሔር አንተ ግን በትምህርቴና በጠባይህ ተከተለኝ ያስተማርኩህን አፋጥን ለእግዚአብሔር ራስህን የተመረጥክ ታደርጋለህ ክቡር ወንጌላዊ ሆይ አንተ የልዑል ጠባቂ (አገልጋይ) ነህ የእግዚአብሔር ሰው ማርቆስ ሆይ በኀይል ላይ አንድነትን የያዝክ ሆንከ » በማለት መስክሮለታል፡፡ማርቆስ ማለት ንህብ ማለት ነው፡፡ ንህብ ሁሉን እንደሚቀስም እሱም ቀድሞ ከክርስቶስ ኋላ ከሐዋርያት ተምሯልና፡፡ አንድም ልዑክ ማለት ነው፡፡ ለስብከተ ወነንጌል ይፋጠናልና፡፡ ማርቆስ አንበሳ ማለት ነው፡፡ አንበሳ ለላም ጌታው ነው ይሰብረዋል እሱም በግብጽ አምልኮተ ጣዖትን አጥፍቷልና፡፡ሐዋርያት ይህን ዓለም ዕጣ በጣ ብለው ተካፍለው ለማስተማር በሚወጡበት ጊዜ ለቅዱስ ጴጥሮስ ሮም በዕጣ ደርሳዋለች በተደራቢነትም ግብጽም ደርሳዋለች፡፡ ለአርእድት ግን ዕጣ የላቸውም አንዱም ሁለቱም እየሆኑ አንዱን ሐዋርያ አንዱም ሁለቱም አንዱን ሐዋርያ ተከትለው ሄዷል ግብጽን ለማርቆስ ሰጥቶት እሱም ሮም ወርዷል፡፡ማርቆም ከዚህ ገብቶ ጌታ ከጽንስ ጀምሮ ያደረገውን ታምራት ያስተማረውን ትምህርት የሠራውን ትሩፋት ቢነግራቸው ከአምልኮተ ጣዖት ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር ከገቢረ ኃጢአት ወደ ገቢረ ጽድቅ ተመለሱ አመኑ ተጠመቁ፡፡“ዕርቃኑን በነጠላ የሸፈነ አንድ ጎበዝ ይከተለው ነበር ጎበዛዝቱም ያዙት እርሱ ግን ነጠላውን ትቶ ዕራቁቱን ሸሸ።” (የማርቆስ ወንጌል ምዕራፍ 14፡51) በአራቱ ወንጌል ላይ ስለ ቅዱስ ማርቆስ የተነገረው ቃል ይህ እንደሆነ በብዙዎች ሊቃውንት ዘንድ ይታመናል፡፡ቅዱስ ማርቆስ የቅዱስ ጳውሎስ ደቀመዝሙር እንደነበረ በኋላም ከአጎቱ ከበርናባስ ጋር እንዳገለገለ ቅዱሳት መጽሐፍት ይመሰክራሉ፡፡ ” በርናባስም ማርቆስ የተባለውን ዮሐንስን ደግሞ ከእነርሱ ጋር ይወስድ ዘንድ አሰበ፤” (የሐዋርያት ሥራ 15:37)ቅዱስ ማርቆስ በአንጾኪያ በርናባስን እያገለገለ አስተምሯል፡፡ (የሐዋርያት ሥራ 12:25) በርናባስ ካረፈ በኋላ ወደ ሮሜ ወደ ቅዱስ ጴጥሮስ ዘንድ ሄዶ ለእርሱ ደቀመዝሙር ሆነ፡፡ ጴጥሮስ የተረጎመለትን ወንጌል በሮሜ አስተመምሯል፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ከፍጹምነት መብቃቱን አውቆ ጵጵስና ሾሞ ከሀገረ ስብከቱ ግብጽን ከፍሎ አስተምር ብሎ ሰጥቶታል ባሕረ ጥበባት ቅዱስ ያሬድ ታሪኩን በዜማ ሲገልጠው እንዲህ ብሏል ፡-« ወረደ ጴጥሮስ ሐቂፎ መንበሮ ለቅዱስ ማርቆስ ወይቤሎ አባ አባ ባርከኒ ብእሲ ወንጌላዊ ዘኩልነ አብ ውስተ ኩሉ ግብፅ አድሚያሃ በስብከትከ ወንጌላዊ ፡፡» ጵጥሮስ የቅዱስ ማርቆስን ዙፋን አቅፎ ወረደ አባት ሆይ የሁላችን ወንጌላዊ ሰው ባርከኝ በስብከትህ በግብፅ በአውራጃዋ ሁሉ ላይ አሰማሁ፡፡ቅዱስ ማርቆስ በስሙ የሚጠራ ወንጌል ጽፏል ቁጥሩም ከ72ቱ አርዕድት ነው፡፡ ወንጌል የሰበከውም በሰማዕትነት ያለፈው በግብፅ ነው፡፡ ክርስትናን በግብፅ የሰበከ ብዙ ተጋድሎ ያደረገ ድንቅ አባት ነው። ቅዱስ ማርቆስም በቤቱ የጌታን ትምህርት ሰምቶ ልቡ ስለተነካ ሁሉንም ነገር ትቶ የክርስቶስን ወንጌለ መንግሥተ ሰማያት ለመስበክ ቆርጦ ተነሳ፡፡ በተጨማሪም የአባቱን እህት ቅዱስ ጴጥሮስ ስላገባት ከእርሱ ጋር በቀላሉ ለመተዋወቅ ችሏል። ጌታ ካረገ በኋላ ሐዋርያት ዓለምን በዕጣ ተከፋፍለው ሲወጡ ከሐዋርያው ከቅዱስ ጳውሎስ ጋር በመጀመሪያው ጉዞ በ46 ዓ.ም ለስብከተ ወንጌል ወጥቶ ነበር። ነገር ግን እናቴ ናፈቀችኝ ብሎ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሰ። ከዚያም ከሐዋርያው ከቅዱስ ጴጥሮስ ጋር መኖር ጀመረ። ከቅዱስ ጴጥሮስ ጋር በመሆን በታናሿ እስያ አድርገው እስከ ሮም ድረስ ወንጌልን አስተምረዋል።

ቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ Read More »

Scroll to Top