በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት

Public Relation

የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጽሕፈት ለጪጩ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን የሰበካ ጉባኤ ቋሚ ፀሐፊ ከዚህ በታች ባለው ክፍት የሥራ መደብ መስፈርቱን የሚያሟላ ሠራተኛ አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል!

ኤክቱስ የካቲት 9/2018 ዓ.ም

የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጽሕፈት ለጪጩ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን የሰበካ ጉባኤ ቋሚ ፀሐፊ ከዚህ በታች ባለው ክፍት የሥራ መደብ መስፈርቱን የሚያሟላ ሠራተኛ አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል! Read More »

የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጽሕፈት ከዚህ በታች ባለው ክፍት የሥራ መደብ መስፈርቱን የሚያሟላ ሠራተኛ አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል!

ኤክቱስ የካቲት 9/2018 ዓ.ም

የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጽሕፈት ከዚህ በታች ባለው ክፍት የሥራ መደብ መስፈርቱን የሚያሟላ ሠራተኛ አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል! Read More »

ለሦስት ወራት መጠነኛ ዕድሳት ሲደረግለት የቆየው የሻራ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ገሪማ ቡራኬ ተከናወነ!

ኤክቱስ የካቲት 08/2018 ዓ.ም በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት በዲላና ወናጎ ወረዳ ቤተ ክህነት የሻራ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ለሦስት ወራት ያኽል መጠነኛ ዕድሳት ሲደረግለት ቆይቶ በብፁዕ አቡነ ገሪማ የሀገረ ስብከቱ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ቡራኬ ተከናውኗል። በዕለቱ ብፁዕነታቸውን ጨምሮ የሀገረ ስብከቱ መንፈሳዊ ትምህርትና የካህናት አገልግሎት ክፍል ኃላፊ መልአከ ሰላም ቆሞስ አባ ዮሐንስ ምሕረቱ፣ የደብሩ አስተዳዳሪ ሊቀ ስዩማን ቀሲስ ምሕረት፣ የአድባራት አስተዳዳሪዎች፣ ካህናትና ዲያቆናት ተገኝተዋል።

ለሦስት ወራት መጠነኛ ዕድሳት ሲደረግለት የቆየው የሻራ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ገሪማ ቡራኬ ተከናወነ! Read More »

Patriarchate Delegation Conducts Extensive Field Visit Led by His Grace Abune Gerima

​Ichthus Dilla, February 12, 2026 (Yekatit 5, 2018 EC) ​A high-level delegation from the Patriarchate General Secretariat of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church, led by His Grace Abune Gerima, Bishop of the Diocese of Gedeo, Kore, and Burji and member of the Holy Synod, conducted an extensive field visit to various development projects across the diocese. ​The tour commenced at the Andida Traditional School of Excellence (Abnet School), where the delegation observed the teaching-learning process of the residential students. They also inspected the poultry and beekeeping projects, the students’ and teachers’ dormitories, the dining facilities, classrooms, and the administrative office. Following this, the delegation visited the beekeeping initiatives and the Enset and coffee plantations at the Dilla Dama St. George Church. ​The visit continued with an inspection of the current construction progress of the Diocesan Residence (Menbere Ppizna). Additionally, the delegation toured the water and poultry projects, as well as the school located at the Dilla Debre Ghenet St. Michael Church. ​Furthermore, the delegation visited the newly constructed administrative office and the parish school at the Dilla Second Gethsemane Ba’ata Le-Mariam Church, including the specific site designated for the Diocese’s upcoming new project. The field visit concluded at the Diocesan Headquarters. ​During the visit, Memhir Daniel Seifemichael, Head of the Research and Development Department at the Patriarchate and Communications Head of the Holy Synod Office, expressed his admiration for the Diocese’s exceptional efforts in fulfilling the mission of the Holy Church. He pledged continued support from the Patriarchate to sustain and enhance these services. ​In his closing remarks, His Grace Abune Gerima extended his gratitude to the delegation for their active participation throughout the training program and for their dedication in visiting the various Diocesan development activities.

Patriarchate Delegation Conducts Extensive Field Visit Led by His Grace Abune Gerima Read More »

ከጠቅላይ ቤተ ክህነት የመጡ ልዑካን በብፁዕነታቸው መሪነት የመስክ ጉብኝት አደረጉ!

ኤክቱስ የካቲት 4/2018 ዓ.ም ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የመጡ ልዑካን በብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል መሪነት በሀገረ ስብከቱ የሠሩ በርካታ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል። በመጀመርያ በአንዲዳ የሚገኘው የአዳሪ የአብነት ትምህርት ቤት የመማር ማስተማር ሂደት፣ የዶሮና የንብ ፕሮጀክቶች፣ የደቀ መዛሙርትና የመምህራን የማደርያ የመመገቢያ እና የመማርያ ክፍሎች እንዲሁም ጽሕፈት ቤት ከተጎበኘ በኋላ የዲላ ዳማ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የሚገኘው የንብ ማነብ ሥራ እንዲሁም የእንሰትና የቡና ልማቶች ተጎብኝተዋል። በመቀጠል ሀገረ ስብከቱ የሚያስገነባው መንበረ ጵጵስና አሁናዊ ሁኔታ፣ የዲላ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን የሚገኘው የውኃና የዶሮ ፕሮጀክቶች እንዲሁም ትምህርት ቤት ተጎብኝቷል። እንዲሁም በዲላ ዳግማዊት ጌቴሴማኒ በዓታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን አዲሱ ጽሕፈት ቤት፣ የደብሩ ትምህርት ቤት እና ሀገረ ስብከቱ አዲስ ፕሮጀክት ለመሥራት ከደብሩ የወሰደው ቦታዎች ከተጎበኙ በኋላ የሀገረ ስብከቱ ጽሕፈት ተጎብኝቷል። መምህር ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤል የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የጥናትና ምርምር መምሪያ ኃላፊ እና የቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤት የኮሚኒኬሽን ኃላፊ በበኩላቸው ሀገረ ስብከቱ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ተልእኮ ለመፈጸም እያደረገ ያለውን ከፍተኛ ጥረት አድንቀው ይህንን አገልግሎት ለመደገፍ ከሀገረ ስብከቱ ጎን እንደሚቆሙ ቃል ገብተዋል። በመጨረሻም ብፁዕነታቸው ልዑካኑ ከሥልጠናው ጀምሮ የነበራቸውን ቆይታ አንስተው እንዲሁም የሀገረ ስብከቱን ሥራዎች ዞረው ስለጎበኙ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ከጠቅላይ ቤተ ክህነት የመጡ ልዑካን በብፁዕነታቸው መሪነት የመስክ ጉብኝት አደረጉ! Read More »

Patriarchate Delegation Led by His Grace Visits Development Projects at Dilla Debre Selam St. Urael Church

​Ichthus Dilla, February 11, 2026 (Yekatit 4, 2018 EC) ​Following the conclusion of the capacity-building training in the Diocese of Gedeo, Kore, and Burji, a high-level delegation from the Patriarchate General Secretariat, led by His Grace Abune Gerima, Bishop of the Diocese, conducted a field visit to various development projects at the Dilla Debre Selam St. Urael Church. ​During the visit, the delegation toured several integrated initiatives within the church premises, including: ​It was noted that these development projects demonstrate the parish’s commitment to self-sufficiency, enabling it to support its spiritual missions independently while creating job opportunities for the local community. ​The delegation praised the parish for its dual focus on spiritual ministry and socio-economic development, describing it as an exemplary model for other cathedrals and monasteries across various dioceses. Furthermore, they commended the projects’ role in strengthening the Church’s financial capacity and their significant contribution to environmental conservation in the region.

Patriarchate Delegation Led by His Grace Visits Development Projects at Dilla Debre Selam St. Urael Church Read More »

በብፁዕነታቸው መሪነት የጠቅላይ ቤተ ክህነት ልዑካን በዲላ ደብረ ሰላም ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን የሚገኙ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ!

ኤክቱስ የካቲት 3/2018 ዓ.ም ​በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ሲሰጥ የነበረው የሥልጠና መርሐ ግብር መጠናቀቁን ተከትሎ በብፁዕ አቡነ ገሪማ የሀገረ ስብከቱ ጳጳስ መሪነት የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ልዑካን በዲላ ደብረ ሰላም ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን የሚገኙ ዘርፈ ብዙ የልማት ሥራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። ​በጉብኝቱ ወቅት ልዑካኑ በደብሩ ቅጥር ግቢ ውስጥ የሚገኙትን የዳቦ ቤት አገልግሎት፣ የቡና ተክል ልማት እንዲሁም የብርቱካን፣ የፓፓያ እና የንብ ማነብ ወዘተ… የግብርና ምርቶችን ተመልክተዋል። እነዚህ የልማት ሥራዎች ደብሩ መንፈሳዊ አገልግሎቱን በራሱ አቅም ለመደገፍና ለአካባቢው ማኅበረሰብም የሥራ ዕድል ለመፍጠር እያደረገ ያለውን ጥረት የሚያሳዩ መሆናቸው ተገልጿል። ​ልዑካኑ ደብሩ ካለው መንፈሳዊ አገልግሎት ጎን ለጎን እንዲህ ያሉ የልማት ሥራዎች ላይ መሰማራቱ በሌሎች አህጉረ ስብከት ለሚገኙ አድባራትና ገዳማት አርአያ የሚሆን ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። ይህም የቤተ ክርስቲያኒቱን የኢኮኖሚ አቅም ከማጠናከር ባሻገር የአካባቢውን የተፈጥሮ ሀብት ለመጠበቅ ያለውን ፋይዳ አድንቀዋል።

በብፁዕነታቸው መሪነት የጠቅላይ ቤተ ክህነት ልዑካን በዲላ ደብረ ሰላም ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን የሚገኙ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ! Read More »

Integrated Training Led by His Grace Abune Gerima Successfully Concluded

​Ichthus February 11, 2026 (Yekatit 4, 2018 EC) ​In accordance with the resolution passed by the Holy Synod of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church, the capacity-building training organized by the Patriarchate General Secretariat in collaboration with the Diocese of Gedeo, Kore, and Burji has been successfully concluded. The program was designed to modernize the Church’s structural operations and empower clergy and staff through professional knowledge. ​During the sessions, Memhir Daniel Seifemichael, a delegate from the Patriarchate General Secretariat, provided detailed briefings on the organization of the Parish Council (Sebeka Gubae), the implementation of the Kale Awadi (the Church’s constitution), performance reporting, social media utilization, and property management. Additionally, Melake Mihret Amha Mekonnen delivered an extensive presentation regarding the Church’s administrative hierarchy and operational procedures. ​The participants engaged in in-depth discussions on these topics, exchanging ideas with the trainers on operational challenges and potential strategic solutions. It was noted that the forum significantly helped bridge the gap between theoretical training and practical field application. ​At the conclusion of the program, a brief position statement was presented, reflecting the readiness of the trainees to implement their new skills. ​The closing ceremony was hosted by Melake Haywet Birhanu Kifle, the Diocesan General Manager. In his fatherly apostolic exhortation, His Grace Abune Gerima, Bishop of the Diocese and member of the Holy Synod, urged the trainees to translate the knowledge gained into action and to fulfill the Church’s mission with integrity. His Grace concluded the program with a prayer and expressed his gratitude to all the faithful who contributed to the success of the training.

Integrated Training Led by His Grace Abune Gerima Successfully Concluded Read More »

በብፁዕ አቡነ ገሪማ መሪነት ሲሰጥ የነበረው የተቀናጀ ሥልጠና በስኬት ተጠናቀቀ!

ኤክቱስ የካቲት 3/2018 ዓ.ም ​የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ውሳኔ መሠረት የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ከጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጋር በመተባበር ሲሰጥ የነበረው የአቅም ግንባታ ሥልጠና ተጠናቋል። መርሃ ግብሩ የቤተ ክርስቲያኒቱን መዋቅራዊ አሠራር ለማዘመንና አገልጋዮችን በዕውቀት ለማነጽ ታቅዶ የተከናወነ ነው። ​በሥልጠናው ወቅት ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ልዑክ መምህር ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤል ስለ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ አደረጃጀት፣ ስለ ቃለ ዐዋዲ አፈጻጸም እንዲሁም ስለ ሥራ ክንውንና ሪፖርት አቀራረብ፣ ስለ ማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃቀምና ስለንብረት አስተዳደር ዝርዝር ማብራሪያ ሰጥተዋል። መልአከ ምሕረት አምሃ መኳንንት በበኩላቸው ስለ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደራዊ መዋቅርና አሠራር ዙሪያ ሰፊ ግንዛቤ ማስጨበጫ አቅርበዋል። ​ሠልጣኞቹ በቀረቡት በእነዚህ ርእሰ ጉዳዮች ዙሪያ ጥልቅ ውይይት ያደረጉ ሲሆን፣ በሥራ ላይ የሚያጋጥሙ ችግሮችንና የመፍትሔ አቅጣጫዎችን በማንሳት ከአሰልጣኞቹ ጋር ሰፊ የሃሳብ ልውውጥ አድርገዋል። ይህ የውይይት መድረክ በንድፈ ሐሳብ የተሰጠው ሥልጠና በተግባር ካለው አሠራር ጋር እንዲዛመድ ትልቅ እገዛ ማድረጉ ተገልጿል። ​በሥልጠናው ማጠቃለያ ላይ የሰልጣኞችን ዝግጁነት የሚያሳይ አጭር የአቋም መግለጫ ቀርቧል። በመጨረሻም በሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ሕይወት ብርሃኑ ክፍሌ ጋባዥነት ብፁዕ አቡነ ገሪማ የሀገረ ስብከቱ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ባስተላለፉት አባታዊ ቃለ ምዕዳን ሠልጣኞች በውይይቱና በሥልጠናው የቀሰሙትን ዕውቀት ወደ ተግባር በመለወጥ የቤተ ክርስቲያንን ተልዕኮ በታማኝነት እንዲወጡ አሳስበዋል። በተጨማሪም ለሥልጠው መሳካት አስተዋጽዖ ላደረጉ የቤተ ክርስቲያን ልጆች ምሥጋናቸውን አቅርበው መርሐ ግብሩን በጸሎት ፈጽመዋል።

በብፁዕ አቡነ ገሪማ መሪነት ሲሰጥ የነበረው የተቀናጀ ሥልጠና በስኬት ተጠናቀቀ! Read More »

H.G. Abune Gerima Leads a Field Visit of Key Diocesan Projects with Muhaze Tibebat Daniel Kibret

​Ektus, February 9, 2026 ​Led by His Grace Abune Gerima, Bishop of the Gedeo, Kore, and Burji Diocese, Muhaze Tibebat Daniel Kibret, Advisor to the Prime Minister and Chairperson of the EBC Board, conducted an extensive visit to various developmental projects within the Diocese. ​The visit commenced at the Andida Residential School of Traditional Ecclesiastical Studies (Abinet School). The delegation observed the teaching-learning process and toured self-sufficiency agricultural initiatives, including a poultry project, as well as classrooms, dining facilities, dormitories, and administrative offices. Subsequently, they visited Enset cultivation and beekeeping projects at Dama Saint George Church, followed by an inspection of the Bishop’s Residence (Menbere Ppisna) building currently under construction within the premises of Dilla Debre Gnet Saint Michael Church. ​The tour concluded with an observation of the water and poultry projects also located at Dilla Debre Gnet Saint Michael Church. At the end of the visit, Muhaze Tibebat Daniel Kibret commended the Church’s multifaceted development efforts aimed at community service and financial self-reliance.

H.G. Abune Gerima Leads a Field Visit of Key Diocesan Projects with Muhaze Tibebat Daniel Kibret Read More »

Scroll to Top