በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት

Uncategorized

በብፁዕነታቸው መሪነት ሙሐዘ ጥበባት ዳንኤል ክብረት በሀገረ ስብከቱ የሚከናወኑ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ!

​ኤክቱስ የካቲት 2/2018 ዓ.ም በብፁዕ አቡነ ገሪማ ​የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል መሪነት፣ የጠቅላይ ሚኒስትር የማኅበራዊ ዘርፍ አማካሪና የኢቢሲ ቦርድ ሰብሳቢ ክቡር ሙሐዘ ጥበባት ዳንኤል ክብረት በሀገረ ስብከቱ የሚከናወኑ ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል። ​በመጀመሪያነት የተጎበኘው በአንዲዳ የሚገኘው የአዳሪ የአብነት ትምህርት ቤት ሲሆን፤ የመማር ማስተማር ሂደቱ፣ የአብነት ትምህርት ቤቱ ራሱን ለማስቻል ከሚሠሩ የግብርና ሥራዎች መካከል የዶሮ ፕሮጀክት፣ እንዲሁም የመማርያ፣ የመመገቢያ፣ የማደርያ እና የጽሕፈት ቤት ክፍሎች ተጎብኝተዋል። በመቀጠልም በዳማ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የሚገኘው የእንሰት ልማትና የንብ ማነብ ሥራዎች የተጎበኙ ሲሆን፤ ሀገረ ስብከቱ የሚያስገነባው የመንበረ ጵጵስና ሕንጻ ግንባታም ተመልክተዋል። ​በመጨረሻም በዲላ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን የሚሠሩ የውኃ እና የዶሮ ፕሮጀክቶችን የጎበኙ ሲሆን፤ ክቡር ሙሐዘ ጥበባት ዳንኤል ክብረት በጉብኝቱ ማጠቃለያ ላይ ቤተክርስቲያኗ ማኅበረሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግና ራሷን ለመቻል እያከናወነች ያለችውን ዘርፈ ብዙ የልማት እንቅስቃሴ አድንቀዋል።

በብፁዕነታቸው መሪነት ሙሐዘ ጥበባት ዳንኤል ክብረት በሀገረ ስብከቱ የሚከናወኑ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ! Read More »

​H.G. Abune Gerima Receives Muhaze Tibebat Daniel Kibret at His Office!

​Ektus, February 9, 2026 ​His Grace Abune Gerima, Bishop of the Gedeo, Kore, and Burji Diocese and member of the Holy Synod, received Muhaze Tibebat Daniel Kibret, Advisor to the Prime Minister on Social Affairs and Chairperson of the EBC Board, at his office. During the visit, His Grace delivered a detailed presentation regarding the historical background and the current developmental activities of the Diocese. ​In his briefing, His Grace explained that the primary focus and goal of the Diocese is to elevate the Holy Church to a better level. Accordingly, he noted that the Church is currently undertaking various development projects that benefit the community. However, His Grace presented the challenges and resource limitations encountered in these developmental works to the Honorable Minister. ​Following the conclusion of this program, a visit was conducted to the development projects being carried out by the Diocese.

​H.G. Abune Gerima Receives Muhaze Tibebat Daniel Kibret at His Office! Read More »

ብፁዕ አቡነ ገሪማ ሙሐዘ ጥበባት ዳንኤል ክብረትን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ!

ኤክቱስ የካቲት 2/2018 ዓ.ም ብፁዕ አቡነ ገሪማ ​የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል የጠቅላይ ሚኒስትር የማኅበራዊ ዘርፍ አማካሪና የኢቢሲ ቦርድ ሰብሳቢ ክቡር ሙሐዘ ጥበባት ዳንኤል ክብረትን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። በቆይታቸውም ስለ ሀገረ ስብከቱ ታሪካዊ ዳራና አሁናዊ የልማት እንቅስቃሴ ዝርዝር ገለጻ አቅርበውላቸዋል። ​ብፁዕነታቸው በገለጻቸው ወቅት የሀገረ ስብከቱ ትኩረትና ፍላጎት ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ወደተሻለ ደረጃ መሆኑን አብራርተዋል። በዚህም መሠረት ቤተክርስቲያኗ ማኅበረሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ልዩ ልዩ የልማት ፕሮጀክቶችን በማከናወን ላይ እንደምትገኝ አስረድተዋል። ​ይሁን እንጂ በእነዚህ የልማት ሥራዎች ላይ የሚታዩ ተግዳሮቶችንና የግብዓት እጥረቶችን ለክቡር ሚኒስትሩ አቅርበዋል።

ብፁዕ አቡነ ገሪማ ሙሐዘ ጥበባት ዳንኤል ክብረትን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ! Read More »

​Official Sales Announcement

​The modern poultry farming project at Dilla Debre Genet St. Michael Church, under the Gedeo, Kore, and Burji Diocese and the Dilla and Wanago Woreda Bete-Kihnet, is officially presenting its products to the faithful and the local community. ​In line with the Diocese’s initiative to ensure the Holy Church’s self-sufficiency and to serve the public, this project has been realized through the coordination of Laeke Wongel Yared Ademe in partnership with the International Livestock Research Institute (ILRI). We are now offering high-quality, health-compliant, and modernly raised chickens for sale. ​Our products are raised with exceptional care using advanced methods and are supplied directly from the farm to the consumer at highly affordable prices. ​📍 Location: Dilla Debre Genet St. Michael Church Poultry Farm Site ⏰ Sales Dates: February 8–15, 2026 (Yekatit 1–8, 2018 E.C.) during regular working hours. ​“Peace be within thy walls, and prosperity within thy palaces.” (Psalm 122:7)

​Official Sales Announcement Read More »

የሽያጭ ማስታወቂያ

​በጌዴኦ ኮሬና እና ቡርጂ ሀገረ ስብከት በዲላ እና ወናጎ ወረዳ ቤተ ክህነት ስር በሚገኘው በዲላ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ሲከናወን የቆየው የዘመናዊ ዶሮ እርባታ ፕሮጀክት፤ አሁን ላይ ውጤቱን ለምዕመናንና ለአካባቢው ነዋሪዎች ማቅረቡን በደስታ ይገልጻል። ​ይህ የልማት ስራ ሀገረ ስብከቱ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንን በልማት ራሷን ለማስቻልና ማኅበረሰቡን ለማገልገል በጀመረው እንቅስቃሴ መሠረት፤ ዓለም አቀፉ የእንስሳት ምርምር ተቋም “International Livestock Research Institute (ILRI)” ከላዕከ ወንጌል ያሬድ አደመ ጋር በጋራ በመሆን የተከናወነ ሲሆን ጥራት ያላቸውና ለጤና ተስማሚ የሆኑ የሥጋ ዶሮዎችን ለሽያጭ አቅርቧል። ​ምርቶቻችን በዘመናዊ መልክና በከፍተኛ እንክብካቤ ያደጉ፣ እንዲሁም በቀጥታ ከእርባታ ጣቢያው ለተጠቃሚ የሚቀርቡ በመሆናቸው በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲጠቀሙ ተጋብዘዋል። ​📍 የሽያጭ ቦታ፦ ዲላ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን የዶሮ እርባታ ሥፍራ ⏰ የሽያጭ ቀንና ሰዓት፦ ከየካቲት 1 – 8 ቀን 2018 ዓ.ም (ዘወትር በሥራ ሰዓት) ​“በኃይልህ ሰላም ፥ በጌጠኛ ቤትህም ልማት ይሁን” (መዝ 122፥7)

የሽያጭ ማስታወቂያ Read More »

Training on Entrepreneurship and Basic Beekeeping Commences in the Diocese!

​Ecthus: January 26, 2026 (Tir 18, 2018) ​In the Gedeo, Kore, and Burji Diocese, a training program focused on entrepreneurship kicked off today. The initiative aims to empower local churches (Adbarat) to become self-reliant, move away from dependency, and enhance their creative business skills. Scheduled to run for three consecutive days until January 20, the training is part of a strategic plan designed for staff and representatives of churches under the Dilla and Wanago (Episcopal Seat) District Administrations. ​The opening session was attended by high-ranking officials, including Melake Haywot Birhanu Kifle, General Manager of the Diocese; Melake Birhan Atnafu Mamo, General Secretary of the Diocese; various diocesan department heads; the General Manager of the District Administration; and administrators and representatives of several local churches. ​The training is being conducted by ICIPE (International Centre of Insect Physiology and Ecology), a non-governmental international organization renowned for its expertise in beekeeping, sericulture (silk farming), and renewable energy. Leveraging its extensive experience, ICIPE is sharing vital knowledge with church ministers and staff. While today’s session focused on entrepreneurship and skill development, the upcoming days are expected to cover practical, hands-on training in basic beekeeping. ​The primary objective of this training is to enable the Holy Church to become self-sufficient through various developmental sectors. This shift is intended to ensure that the “Mudaye Mitswat” (alms collection) is dedicated solely to its intended charitable and spiritual purposes. Participants have been directed to implement the knowledge gained within their respective local churches and take a leading role in efforts to bolster the institution’s internal revenue.

Training on Entrepreneurship and Basic Beekeeping Commences in the Diocese! Read More »

በሀገረ ስብከቱ የሥራ ፈጠራ ማዳበርና መሠረታዊ የንብ ማነብ ሥልጠና ተጀመረ!

ኤክቱስ በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት፤ አድባራት ከልመና እንዲላቀቁ፣ በገቢ ራሳቸውን እንዲችሉና የሥራ ፈጠራ ችሎታን ለማዳበር በሥራ ፈጠራ ዙሪያ የሚያተኩር ሥልጠና በዛሬው ዕለት ተጀምሯል። እስከ ጥር 20 ቀን ድረስ ለሦስት ተከታታይ ቀናት የሚቆየው ይህ ሥልጠና፤ በዲላና በወናጎ (በመንበረ ጵጵስና) ወረዳ ቤተ ክህነት ስር ለሚገኙ አድባራት ሠራተኞችና ተወካዮች ታስቦ የተዘጋጀ የዕቅድ አካል ነው። በዛሬው መርሐግብር ላይ የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ሕይወት ብርሃኑ ክፍሌ፣ የሀገረ ስብከቱ ዋና ጸሐፊ መልአከ ብርሃን አጥናፉ ማሞ፣ የሀገረ ስብከቱ የክፍል ኃላፊዎች፣ የወረዳ ቤተ ክህነቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የአድባራት አስተዳዳሪዎችና ተወካዮች ተገኝተዋል። ይህንን ሥልጠና እየሰጠ የሚገኘው በንብ ማነብ፣ በሐር ትል እና በታዳሽ ኃይል ዙሪያ የሚንቀሳቀሰው ICIPE (International Centre of Insect Physiology and Ecology) የተባለ ዓለም አቀፍ ድርጅት ነው። ድርጅቱ በዘርፉ ያለውን የረዥም ጊዜ ተሞክሮ ለቤተክርስቲያኗ አገልጋዮችና ሠራተኞች እያካፈለ የሚገኝ ሲሆን በዛሬው ውሎ በሥራ ፈጠራ ላይ ትኩረት ተሰጥቶ ከዋለ በኋላ በቀጣዮቹ ቀናት ደግሞ በመሠረታዊ የንብ ማነብ ሙያ ላይ ተግባራዊ ትምህርቶች እንደሚሰጡ ይጠበቃል። የዚህ ሥልጠና ዋና ዓላማ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በተለያዩ የልማት መስኮች ተሰማርታ በገቢ ራሷን እንድትችል ማስቻል ነው። ይህም በቤተክርስቲያን የሚሰበሰበው “ሙዳየ ምጽዋት” ለታለመለት ለምጽዋት ተግባር እንዲውል ለማድረግ የሚረዳ መሆኑ ተመልክቷል። ተሳታፊዎችም ከሥልጠናው የሚገኘውን ዕውቀት ወደየአጥቢያቸው በመውሰድ ተግባራዊ እንዲያደርጉና የተቋሙን የውስጥ ገቢ ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ግንባር ቀደም ተሳታፊ እንዲሆኑ አቅጣጫ ተቀምጧል።

በሀገረ ስብከቱ የሥራ ፈጠራ ማዳበርና መሠረታዊ የንብ ማነብ ሥልጠና ተጀመረ! Read More »

1,683 New Believers Receive the Grace of Divine Sonship During Epiphany!

​ICTHUS January 21, 2026 (Tir 13, 2018 EC)​ In the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church, within the Diocese of Gedeo, Kore, and Burji, 1,683 new believers were baptized and received the Grace of Divine Sonship during the celebrations of the Epiphany (Timket) and Kana Ze Gelila of our Lord and Savior Jesus Christ. ​The distribution of the new converts across the district (Woreda Bete kihnet) is as follows: 408 within the Dilla and Wonago Bete kihnet (the See of the Bishopric), 524 in the Yirgacheffe district, 191 in the Kochore, Gedeb, and Chorso district, 88 in the Bule and Reppe district, 301 in the Kore zone district, and 171 in the Burji zone district. All have received the Sacrament of Baptism and the Grace of Sonship. ​The Diocese is currently undertaking extensive work by assigning gospel preachers who teach in local languages to reach and baptize non-orthodoxy in the region. ICHTHUS GEDEO KORE AND BURJI DIOCESE PUBLIC RELATION DEPARTMENT

1,683 New Believers Receive the Grace of Divine Sonship During Epiphany! Read More »

አንድ ሺህ ስድስት መቶ ሰማንያ ሦስት አዳዲስ አማንያን በበዓለ ጥምቀት ተጠምቀው የሥላሴን ልጅነት አገኙ!

ኤክቱስ ጥር 13/2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት በጌታችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀትና የቃና ዘገሊላ በዓላት ላይ አንድ ሺህ ስድስት መቶ ሰማንያ ሦስት አዳዲስ አማንያን ተጠምቀው የሥላሴን አግኝተዋል። በመንበረ ጵጵስናና ወናጎ ወረዳ ቤተ ክህነት 408፣ በይርጋጨፌ ወረዳ ቤተ ክህነት 524፣ በኮቾሬ ገደብና ጮርሶ ወረዳዎች ቤተ ክህነት 191፣ በቡሌና ረጴ ወረዳዎች ቤተ ክህነት 88፣ በኮሬ ወረዳ ቤተ ክህነት 301፣ በቡርጂ ወረዳ ቤተ ክህነት 171 አዳዲስ አማንያን ተጠምቀው የሥላሴን ልጅነት አግኝተዋል። ሀገረ ስብከቱ ኢ-አማንያንን ለማስጠመቅ በአከባቢው ቋንቋ የሚያስተምሩ ሰባኪያነ ወንጌል በመመደብ በርካታ ሥራዎችን እየሠራ ይገኛል።

አንድ ሺህ ስድስት መቶ ሰማንያ ሦስት አዳዲስ አማንያን በበዓለ ጥምቀት ተጠምቀው የሥላሴን ልጅነት አገኙ! Read More »

አንድ መቶ ሃያ አዳዲስ አማንያን በብፁዕ አቡነ ገሪማ ተጠምቀው የሥላሴን ልጅነት አገኙ!

ኤክቱስ ጥር 11/2018 ዓ.ም በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት በመንበረ ጵጵስናና ወናጎ ወረዳ ቤተ ክህነት በዲላ ከተማ በጌታችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል ዕለት አንድ መቶ ሃያ አዳዲስ አማንያን በብፁዕ አቡነ ገሪማ የሀገረ ስብከቱ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ተጠምቀው የሥላሴን ልጅነት አግኝተዋል። በዕለቱ ከአንድ መቶ ሃያ ተጠማቂያን መካከል አንድ መቶ አስሩ ኢ-አማንያን ሲሆኑ አስሩ ደግሞ ሕጻናት መሆናቸው ተገልጿል።

አንድ መቶ ሃያ አዳዲስ አማንያን በብፁዕ አቡነ ገሪማ ተጠምቀው የሥላሴን ልጅነት አገኙ! Read More »

Scroll to Top