በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት

Public Relation

3372 አዳዲስ አማንያንን ማስጠመቁን የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ገለጸ!!

ኤክቱስ ጥቅምት 5/2018 ዓ.ም ከተጀመረ ሁለተኛ ቀኑን በያዘው ፵፬ተኛው ዓለም አቀፍ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ላይ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት በ2017 በጀት ዓመት ያሳካውን የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ተልእኮ ሪፖርት የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ሕይወት ብርሃኑ ክፍሌ አቅርበዋል። በሪፖርቱ እንደተገለጸው ሀገረ ስብከቱ በበጀት ዓመቱ ብፁዕ አቡነ ገሪማ የቤተ ክርስቲያንን ልጆች በማስተባበር የተዘጉ አብያተ ክርስቲያናትን እንዳስከፈቱ የተገለጸ ሲሆን በሁሉም ወረዳ ቤተ ክርስቲነት በመዘዋወር ሀዋርያዊ አገልግሎታቸውን መፈጸማቸውም ተገልጿል። የአብነት ትምህርት ቤትን በተመለከተ በአንዲዳ ለመጀመርያ ዙር የአብነት ተማሪዎች የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን በሟሟላት እና የቅዳሴ መምህር በመቅጠር ትምህርት እንዲሰጥ እንደተደረገ ተገልጿል። በተጨማሪም በሀገረ ስብከቱ ስብከተ ወንጌልን ለማስፋፋት ከ20 በላይ በተመረጡ አብያተ ክርስቲያናት ሕዝባዊ መንፈሳዊ ጉባኤያት የተደረገ ሲሆን በስድስቱም ወረዳ ቤተ ክህነቶች ካለፈው ዓመት በተሻለ መልኩ 3372 አዳዲስ አማንያን መጠመቃቸውን ገልጸዋል።

3372 አዳዲስ አማንያንን ማስጠመቁን የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ገለጸ!! Read More »

ብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሥር በሚገኘው የአረርቲ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን በደረሰው አደጋ የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገለጹ!!

“ይቤዙ እግዚአብሔር ነፍሰ አግብርቲሁ ወኢይኔስሑ ኩሎሙ እለ ይትዌከሉ ቦቱ – የባርያዎቹን ነፍስ እግዚአብሔር ይቤዣል በርሱም የሚያምኑ ሁሉ አይጸጸቱም”መዝ 33፥22 በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ምንጃር ሸንኮራ ወረዳ ሥር በሚገኘው አረርቲ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም በሕንጻ ግንባታ ምክንያት ለፊኒሽንግ ሥራ የተረበረበ እንጨት ተደርምሶ እስካሁን በሚያሳዝን ሁኔታ በውል ያልታወቁ ወገኖቻችን ሕይወታቸው ማለፉን ከሀገረ ስብከቱ ሚዲያ ስንሰማ እጅግ ከልባችን አዝነናል። ለሞቱት ወገኖቻችን እግዚአብሔር አምላካችን ሀገረ ሕይወትን መንግስተ ሰማያትን እንዲያወርስልን ከቅዱሳን ማኅበር እንዲደምርልን፤ ለቤተሰቦቻቸው መጽናናትን እንዲልክን ጸሎታችን ነው። እግዚአብሔር ሀገራችንን ይባርክ! አባ ገሪማየጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባልመስከረም 21/2018 ዓ.ም

ብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሥር በሚገኘው የአረርቲ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን በደረሰው አደጋ የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገለጹ!! Read More »

ቃለ በረከት ዘብፁዕ አቡነ ገሪማ ጳጳስ ዘተናገሮ በበዓለ ርእሰ ዐውደ ዓመት ዘዕሥራ ምእት ዐሠርቱ ወሰመንቱ ዓመተ ምሕረት

ቃለ በረከት ዘብፁዕ አቡነ ገሪማ ጳጳስ ዘተናገሮ በበዓለ ርእሰ ዐውደ ዓመት ዘዕሥራ ምእት ዐሠርቱ ወሰመንቱ ዓመተ ምሕረት

ኤክቱስ ጳጉሜን 5/2017 ዓ.ም

ቃለ በረከት ዘብፁዕ አቡነ ገሪማ ጳጳስ ዘተናገሮ በበዓለ ርእሰ ዐውደ ዓመት ዘዕሥራ ምእት ዐሠርቱ ወሰመንቱ ዓመተ ምሕረት Read More »

‎ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ለ2018 አዲስ ዓመት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ!

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእስ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ለ2018 ዓ.ም አዲስ ዓመት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። በመልዕክታቸውም ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር ለሚገኙ፣ የሀገሪቱን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ ለቆሙ፤ በሕመም ምክንያት በየፀበሉና በየሆስፒታሉ ለሚገኙ ብሎም የሕግ ታራሚዎች ሆነው በየማረሚያ ቤቱ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያት፤ “እንኳን ለሁለት ሺሕ ዐሥራ ስምንት ዓመተ ምህረት የርእሰ ዐውደ ዓመት በዓል አደረሳችሁ!” ሲሉ የመልካም ምኞት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።‎‎ቅዱስነታቸው በአባታዊ መክልዕታቸው፤ “የሰው ልጅ ከፍጥረታት ሁሉ የተለየ ክብርና ደረጃ እንዳለው በቅዱስ መጽሐፍ በተደጋጋሚ ተገልጾአል፣ ልዩ የሚያደርገውም ከአፈጣጠሩ ጀምሮ ነው፣ ሰው ልዩ ፍጡር መሆኑን ከሚገለጽባቸው መካከል እግዚአብሔር በሦስትነቱ “ሰውን በአርአያችንና በአምሳላችን እንፍጠር በሚል ልዩ አገላለጽ መፈጠሩ፣ አፈጣጠሩም በእግዚአሔር መልክና አምሳል መሆኑ፣ በእግዚአብሔር እፍታ ሕያው ነፍስ እንዲኖረው መደረጉ፤ በሥልጣንም የፍጥረታት ሁሉ የበላይ ሆኖ መሾሙ ከሌሎች ፍጥረታት ልዩ ያደርገዋል” ብለዋል፡፡‎‎”እኛ ሰዎች የእግዚአብሔር ክብር መገለጫ ሆነን እንድንኖር በእግዚአብሔር ስንፈጠር በሕይወት እንድንኖር ነው፣ እግዚአብሔር በምድር ላይ በሕይወት ይኖሩ ዘንድ ሰውን ከአንድ ፈጠረ የሚለው መጽሐፍ ቅዱሳዊ አስተምህሮም ይህንን ያመለክታል” ሲሉም ተናግረዋል፡፡ አክለውም “ሰዎች በምድር ላይ በሕይወት እንዲኖሩ የተፈጠሩ ሆነው እያለ በሕይወት እንዳይኖሩ ማድረግ ከፈቃደ እግዚአብሔር ጋር መጋጨትን ያስከትላል በዘመናችን ዓለማችንን እየፈተነ ያለው ተቀዳሚ ፈተና ሰዎች በሕይወት እንዳይኖሩ የማድረግ ዝንባሌ ነው” ብለዋል።‎‎”እንደዚህ ዓይነቱ ዝንባሌ በዓለም ባይኖር ኖሮ በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ድሆች ባሉበት ዓለም ለሰው ልጅ ሕይወት ማጥፊያ የሚሆን መሳሪያ ለማምረት ቁጥር ስፍር የሌለው ገንዘብ አይወጣም ነበር” በማለትም ቅዱስነታቸው ገልጸዋል።‎‎ስለሆነም በሕይወት እንዲኖር የተፈጠረውን ሰው በሕይወት የመኖር መብቱን ከመንፈግ መቆጠብ የአዲሱ ዓመት ትልቁ አጀንዳ አድርገን ብንወስድ ለሁላችንም ይበጀናል በማለት አባታዊ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።‎‎ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ አክለውም፤ “ለኑሯአችን የሚያስፈልገንን ፍጆታ በበቂ ሁኔታ እንድናገኝ ላባችንን አንጠፍጥፈን መስራት ይገባናል፣ ይህም ከሠራን ያለጥርጥር የምናገኘው ነው፤ ሁለቱም የጎደሉብን በኛ አስተሳሰብ፣ አሠራርና አጠቃቀም እንጂ እግዚአብሔር ሳይፈቅድልን ቀርቶ ወይም ነፍጎን አይደለም”ብለዋል።‎‎ነገር ግን እኛ በምንራመድበት በእግራችን ሥር ያለውን ሀብት ትተን በሩቅ ያለውን ስንመለከት ሁሉን ያጣን ሆነን በችግር ወድቀን እንገኛለን፤ በተለይም እኛ ኢትዮጵያውያን በአሁኑ ጊዜ እየተፈታተነን ያለው ይኸው የተሳሳተ እሳቤ ነው ብለዋል።‎‎”ኢትዮጵያ የሁላችንም ኢትዮጵያውያን አድርገን በማመን በእኩልነት፣ በአንድነትና በስምምነት ከመጠቀም ይልቅ ያ የኔ ነው ያም የኔ ነው በሚል አባባል ምን ያህል ዋጋ እየተከፈለ እንደሆነ እያየን ነው፣ ይህ ግለኝነት ያየለበት አስተሳሰብ ገታ አድርገን በእኩልነትና በአብሮነት የሚያሳድገንን አስተሳሰብ የተሻለ መግባቢያ ሊሆን ይችላል፣ አዲሱ ዓመት በአዲስ እሳቤ ካላጀብነው አዲስ ሊሆን አይችልም” በማለት ገልጸዋል።‎‎ስለሆነም “አዲሱን ዓመት መልካም በሆነ አዲስ ሀሳብ ፣እግዚአብሔርንና ሰውን በሚያገናኝ ቅዱስ ተግባር፣ በልማት፣ በሰላም፣ በፍቅር፣ በዕርቅና በስምምነት እንድንቀበለው” ሲሉ ጥሪያቸውን አስተላልፏል።‎‎አዲሱ ዓመት ለሀገር ሰላምና ልማት፤ ለሕዝቦች አንድነትና ስምምነት እንደዚሁም አለመግባባትን በፍትሕና በዕርቅ ለመፍታት ከልብ የምንተጋበት መልካም የስኬት ዘመን እንዲሆንልን እንጸልይ በማለት ለመላ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት ሁሉ አባታዊ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። ©መረጃው የተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል ነው የማኅበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችንን ይወዳጁ! Facebook https://www.facebook.com/Ge7de12o Telegram https://t.me/Gedeokoreburji Tiktok Tiktok.com/@gedeokoreburji Instagram https://www.instagram.com/gedeokoreburji?igsh=azJrOGdpbDN4cG4= Youtube Website – Eotc-gkb.org

‎ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ለ2018 አዲስ ዓመት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ! Read More »

ለገጠር አብያተ ክርስቲያናት የንዋየ ቅድሳት ድጋፍ ተደረገ!!

በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ሥር ለሚገኙ የንዋየ ቅድሳት እጥረት ላለባቸው የገጠር አብያተክርስቲያናት የንዋየ ቅድሳት ድጋፍ ተደረገ። ድጋፉ በመምህር ያሬድ አደመ በኩል የተደረገ ሲሆን ልብሰ ተክኅኖ፣ ጧፍ፣ እጣን፣ ዘቢብ፣ መጾርና መባረኪያ መስቀሎች፣ በርካታ የቤተ መቅደስ መጻሕፍት፣ የሥጋ ወደሙ ማክበሪያ አጎበር፣ ጸናጽል፣ ማዕፈድ የመሳሰሉ ንዋየ ቅድሳት ድጋፍ ተደርገዋል። ድጋፉን ብፁዕ አቡነ ገሪማ የሀገረስብከቱ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል የተረከቡ ሲሆን ድጋፉን ላደረጉ ምዕመናን ምሥጋና አቅርበዋል።

ለገጠር አብያተ ክርስቲያናት የንዋየ ቅድሳት ድጋፍ ተደረገ!! Read More »

የቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በቆቲ ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን በታላቅ መንፈሳዊ ክብር ተከበረ !!

በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት በመንበረ ጵጵስናና ወናጎ ወረዳ ቤተክህነት ሥር በሚገኘው በቆቲ ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን የቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በታላቅ ድምቀት ተከበረ። መርሐ ግብሩን የመንበረ ጵጵስናና ወናጎ ወረዳ ቤተክህነት ዋና ጸሐፊ ሊቀኀሩያን እሸቱ ዋለ የመሩት ሲሆን ትምህርተ ወንጌል የሰጡትና ለቤተክርስቲያን የልማት ሥራ ያስተባበሩት የሀገረ ስብከቱ የስብከተ ወንጌል ክፍል ኃላፊ ሊቀትጉሃን ቀሲስ ሀብታሙ አበበ ሲሆኑ በትምህርታቸውም ሩፋኤል ማለት እግዚአብሔር ፈዋሽ ነው ማለት መሆኑን የገለጹ ሲሆን ሩፋኤል ማለት ፈታሄ ማኅፀን ማለት ነው ብለዋል፡፡ በመጨረሻም ጸሎት ተደርጎ የበዓሉ ፍጻሜ ይሆናል ።

የቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በቆቲ ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን በታላቅ መንፈሳዊ ክብር ተከበረ !! Read More »

በመምህር ያሬድ አደመ እና በወዳጆቹ ለዳኖ ቡልቶ ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን የንዋየ ቅድሳት ድጋፍ ተደረገ!!

በመምህር ያሬድ አደመ እና በወዳጆቹ ለዳኖ ቡልቶ ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን የንዋየ ቅድሳት ድጋፍ ተደረገ!! በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት በኮሬ ወረዳ ቤተክህነት ሥር ለሚገኘው ለዳኖ ቡልቶ ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን በመምህር ያሬድ እና በወዳጆቹ ለአንድ ሰሞነኛ የሚሆን ሙሉ መቀደሻ አልባሳ፣ የተለያዩ መጽሐፍትና መጽሐፈ ድጓ ሳይቀር ለአብነት ተማሪዎች ጫማ የተደረገውን ድጋፍ ብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል የተረከቡ ሲሆን ድጋፉን ያደረጉትን ሁሉ አመስግነው ድጋፉ ቅድስት ቤተክርስቲያን አገልግሎቷን በተሟላ መልኩ እንድትሰጥ የሚያደርግ በመሆኑ ለሌላው አርአያ መሆኑም ተገልጿል ።

በመምህር ያሬድ አደመ እና በወዳጆቹ ለዳኖ ቡልቶ ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን የንዋየ ቅድሳት ድጋፍ ተደረገ!! Read More »

ከአራቱ ወረዳ ለተውጣጡ ከቋንቋ ሰባኪያነ ወንጌል ጋር ውይይት ተደረገ!!

ከአራቱ ወረዳ ለተውጣጡ ከቋንቋ ሰባኪያነ ወንጌል ጋር ውይይት ተደረገ!! በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ከአራት ወረዳ ቤተክህነት ማለትም ከመንበረ ጵጵስናና ወናጎ፣ ከይርጋጨፌ፣ከኮቸሬና ገደብ ፣ከቡሌና ረጴ ወረዳዎች ከተውጣጡ በጌዴኡፋ ቋንቋ የስብከተ ወንጌል አገልግሎት ከሚሰጡ ሰባኪያነ ወንጌል ጋር ብፁዕ አቡነ ገሪማ የሀገረ ስብከቱ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ጋር ውይይት ተደረገ። ውይይቱ ከቤተክርስቲያን ካህናት ማሰልጠኛ ተመርቀው ወጥተው ምን አከናወኑ፣የስብከተ ወንጌል አገልግሎት ሲሰጡ የገጠማቸው ተግዳድሮት ነበረ፣ለገጠማቸው ችግር የወሰዱት የመፍትሔ ሃሳብ ምን ነበር፣በአገልግሎት የተገኘው ውጤት ምን ነበር፣ያሉትን ለማጽናት የጠፉትን ለመመለስ አዳዲስ ኢአማንያንን ለማምጣት ምን አከናወኑ በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን። ሰባኪያነ ወንጌሉ በአገልግሎት ላይ የገጠማቸውን ችግር ያነሱ ሲሆን መስዋዕትነት እስኪከፍሉ ድረስ ዋጋ መክፈላቸው ሰንበት ት/ቤት ማደራጀት ባዕድ አምልኮ ማጥፋት ብዙ ኢአማኒያን ማስጠመቅ ኮርስ መስጠት በማኀበራዊ ሕይወት መሳተፍ በሀዘንና በደስታ ስብከተ ወንጌል መስጠት የሚሉ የአገልግሎት ተግባራትን የዘረዘሩ ሲሆን። በቀጣይ ከተከናወነው ያልተሰራው ስለሚበዛ በቁጭት በቋንቋ ለማስተማር ቃል ገብተዋል። የሀገረ ስብከቱ ስብከተ ወንጌል ክፍል ኃላፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ሀብታሙ አበበ በሰጡት አስተያየት ለተጠራንበት አገልግሎት ቁርጠኛ መሆን እንደሚገባ ከጠባቂነት መውጣትና በዕቅድና በዓላማ ማገልገል አገልግሎታቸው ሁሉ በውጤት የታጀበ መሆን እንዳለት በተለይ ያሉትን በማጽናትና መጠበቅ የጠፉትን ማምጣት አዳዲስ አማኒያንን ወደ ክርስትና በማምጣት ላይ አገልግሎታቸውን መወጣት እንዳለባቸው አንስተዋል። በመጨረሻም በብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል በማጠቃለያው የስብከተ ወንጌል በሚገባ አገልግሎት አልተፈጸም የቤተክርስቲያንን ተልዕኮ በአግባቡ አውቆ ያለመፈጸም ሰባኪ ከጠባቂነት መውጣት ለዚህ አገልግሎት የተጠራን ባለዕዳዎች መሆንናችንን አንስተው የማሳመኑን የማስተማሩን ሥራ በአግባቡ መወጣት አለብን ብለዋል። በየመንደሩ የስብከተ ወንጌል ኬላ ማቋቋምና አገልግሎትን መፈጸም በማኀበራዊ ሁነቶች ላይ መሳተፍ በቁርጠኝነት ወንጌልን ማገልገል እንደሚያስፈልግ እስከ ሕይወት መስዋዕትነት መክፈል እንደሚገባ አሳስበው በቀጣይ ለአንድ ዓመት የሚቆይ ፕሮጀክት የተወጋጀና የስብከተ ወንጌል አገልግሎት ሥምሪት እንደሚሰጥ በማሳሰብ ውይይቱ ተጠናቋል ።

ከአራቱ ወረዳ ለተውጣጡ ከቋንቋ ሰባኪያነ ወንጌል ጋር ውይይት ተደረገ!! Read More »

በዲላ መዝገበ ምሕረት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን የተዘጋጀው ሁለተኛ ቀን መንፈሳዊ ጉባኤ ተጠናቀቀ።

በዲላ መዝገበ ምሕረት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን የተዘጋጀው ሁለተኛ ቀን መንፈሳዊ ጉባኤ ተጠናቀቀ። በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት በመንበረ ጵጵስናና ወናጎ ወረዳ ቤተ ክህነት በመዝገበ ምሕረት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን በዓለ ጽንሰት በማስመልከት የተዘጋጀው መንፈሳዊ ጉባኤ ሁለተኛ ቀን ተጠናቋል። በጉባኤው የሀገረ ስብከቱ ስብከተ ወንጌል ክፍል ኃላፊ ሊቀ ትጉሃን ሀብታሙ አበበ፣ የወረዳ ቤተ ክህነቱ ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ጠበብት መሪጌታ መሰረት ይልማ፣ የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ምሕረት ቀሲስ ሰናይ፣ ሰባኪያነ ወንጌል እና ዘማሪያን፣ የደብሩ ካህናትና ዲያቆናት፣ በርካታ ምዕመናን ተገኝተዋል። በጉባኤው የበገና ዝማሬ፣ ትምህርተ ወንጌል በተጋባዥ መምህራን፣ ዝማሬ የተሰጠ ሲሆን ጉባኤው ዛሬም እንደሚቀጥል ተገልጾ የመርሃግብሩ ፍጻሜ ሆኗል።

በዲላ መዝገበ ምሕረት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን የተዘጋጀው ሁለተኛ ቀን መንፈሳዊ ጉባኤ ተጠናቀቀ። Read More »

Scroll to Top