ብፁዕ አቡነ ገሪማ የሀገረ ስብከቱ ጳጳስ ከኮምፒተር ባለሙያዎች ጋር ተወያዩ!!
ብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ከዲላ ዩኒቨርስቲ የኮምፒውተር ባለሙያዎች ጋር ተወያዩ። የውይይቱ መሠረታዊ ዓላማ ዘመኑን የዋጀ አገልግሎት ከመስጠትና ከመቀበል አንጻር የኮምፒውተር መሠረታዊ እውቀት መኖር አስፈላጊ መሆኑ ይታወቃል ። ይኸም በሀገረ ስብከቱ ዘመናዊ አገልግሎት ከመስጠት አንጻር ያለውን ክፍተት ለመቅረፍ በቀጣይም ዘመናዊ አሰራር ለመዘርጋት ይቻል ዘንድ የውይይቱ አካል ነበር። ዘመናዊ የኮምፒውተር እውቀት ወረቀት አልባ አገልግሎት እንዲኖር ከማድረጉ በተጨማሪ የኢንተርኔት አገልግሎትን በሚገባ ከተጠቀሙ የመረጃ ልውውጥ የሚያፋጥን መሆኑ እሙን ነው።ይኸንም በቀጣይ የተሻለ አሰራር ለመተግበር የሚያስችል መሆኑ ተመልክቷል ።
ብፁዕ አቡነ ገሪማ የሀገረ ስብከቱ ጳጳስ ከኮምፒተር ባለሙያዎች ጋር ተወያዩ!! Read More »









