በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት

የሀገረ ስብከቱ ግብና ተግባራት

የሀገረ ስብከቱ የቁጥጥር ክፍል ሥራና ኀላፊነት

የሀገረ ስብከቱ የቁጥጥር ክፍል ሥራና ኀላፊነት ፩.ልዩ ልዩ ገቢና ወጪ የተደረገባቸውን ካርኒዎችና ሰነዶች ህጋዊ መሆናቸውን ይመረምራል እንዲሁም ገንዘቡ በትክክል ተቆጥሮ በባንክ መቀመጡን ያረጋግጣል ፡፡ ፪.የሒሳቡ አያያዝ አጠባበቅ ትክክል መሆኑንና አለመሆኑን በዝርዝር መዝግቦ በየሦስት ወር  ለአስተዳደር ጉባኤ ሪፖርት ያቀርባል፡፡ ፫. ከሚመለከታቸው ክፍሎች ጋር የሀገረ ስብከቱን ንብረት በየዓመቱ ኦዲት ያደርጋል፡፡ ፬. በሀገረ ስብከቱ ለዓመት ከተመደበው በጀት በላይ ወጪ እንዳይሆን ይቆጣጠራል፡፡

የሀገረ ስብከቱ የቁጥጥር ክፍል ሥራና ኀላፊነት Read More »

የሀገረ ስብከቱ የመንፈሳዊ ትምህርት ክፍል ሥራና ኀላፊነት

የሀገረ ስብከቱ የመንፈሳዊ ትምህርት ክፍል ሥራና ኀላፊነት ፩.በሀገረ ስብከቱ በሚገኙ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት መንፈሳዊና ዘመናዊ ት/ቤት እንዲቋቋም ያደርጋል እንዲሁም ለተማሪዎችም የሚያስፈልገውን በጀት እንዲመደብ የሚመለከታቸውን ሁሉ ያስተባብራል፡፡ ፪.የትምህርት መስጫ ቦታዎች አመቺ እንዲሆኑና መምህራን ጉባኤያቸውን ሳይፈቱ እንዲያስተምሩ ያደርጋል፡፡ ፫. ቤተ መጻሕፍት እንዲያቋቁሙና ካህናት ዲያቆናት የሰንበት ት/ቤት ተማሪዎች ተገኝተው እንዲያነቡ አስፈላጊው ሁሉ እንዲፈጸም ያደርጋል፡፡ ፬. ህጻናት በሥነ ምግባርና በሃይማኖት ተኮትኩተው እንዲያድጉ ያደርጋል፡፡ ፭. የመማር የማስተማር ሂደት በተሳለጠ መልኩ በቅርበት ሆኖ ይቆጣጠራል፡፡

የሀገረ ስብከቱ የመንፈሳዊ ትምህርት ክፍል ሥራና ኀላፊነት Read More »

የሀገረ  ስብከቱ  የንብረት የንዋየ ቅድሳትና የቅርሳ ቅርስ ክፍል ሥራና ኀላፊነት

የሀገረ  ስብከቱ  የንብረት የንዋየ ቅድሳትና የቅርሳ ቅርስ ክፍል ሥራና ኀላፊነት ፩.የሀገረ ስብከቱ አላቂና ቋሚ ዕቃዎችን የሚንቀሳቀሱና የማይንቀሳቀሱ ንብረቶችን በየአይነታቸው ለይቶ መዝግቦ ይይዛል ፡፡ ወጪ ሆነው ለሥራ የሚሰጡትን ዕቃዎችና ንብረቶች በህጋዊ ሰነድ ያስረክባል፣ወጪ የተደረጉ ንብረቶችን ሥራ ላይ መዋላቸውንና መጠበቃቸውን ይቆጣጠራል ፣የሚመለሱትንም መርምሮ ይረከባል፡፡ ፪. ጥገና የሚያስፈልጋቸውን የሀገረ ስብከቱ ንብረቶችን  በሰዓቱ እንዲጠገኑ ያደርጋል፡፡ ፫. በየዓመቱ የንብረት ቆጠራ ያደርጋል፡፡

የሀገረ  ስብከቱ  የንብረት የንዋየ ቅድሳትና የቅርሳ ቅርስ ክፍል ሥራና ኀላፊነት Read More »

የሀገረ ስብከቱ  የካህናት አገልግሎት ክፍል ሥራና ኀላፊነት

የሀገረ ስብከቱ  የካህናት አገልግሎት ክፍል ሥራና ኀላፊነት ፩. በሀገረ ስብከቱ ሥር ባሉ አድባራትና አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት መንፈሳዊ አገልግሎቶች ትክክለኛውን ሥነ ሥርዓት ይዘው መካሄዳቸውን ይከታታላል ይቆጣጠራል፡፡ ፪. ካህናት የንሰሐ ልጆቻቸን ለመጠበቅ እንዲችሉ ከሚመለከታቸው ክፍሎች ጋር በመቀናጀት  በትምህርተ ወንጌል እንዲሰለጥኑ ያደርጋል ፡፡ ፫.ለክህነት የሚያበቃውን ሙያ ያወቀና ግብረ ገብነቱና መንፈሳዊ ዝንባሌው በካህናትና በምዕመናን የተመሰከረለትን እንዲሁም ወንጌልን ማስተማር የሚችል እንደ የማዕረጋቱ የዲቁናና የቅስና ማዕረግ እንዲቀበል ለሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ያቀርባል፡፡ ፬. ክህነታቸው ያልታወቀና ካህን መነኩሴ ነኝ በሚሉ ላይ ቁጥጥር ያደርጋል፡፡

የሀገረ ስብከቱ  የካህናት አገልግሎት ክፍል ሥራና ኀላፊነት Read More »

የሀገረ  ስብከቱ  የህግ አገልግሎት ክፍል ሥራና ኀላፊነት

የሀገረ  ስብከቱ  የህግ አገልግሎት ክፍል ሥራና ኀላፊነት ፩. ከበላይ አካል የሚወጡ ህጎች ደንቦች ድንጋጌዎች ውሳኔዎችና መመሪያዎች ለካህናትና ለምዕመናን እንዲያውቁትና እንዲያጠኑት ያደርጋል፡፡ ፪. የሀገረ ስብከቱን ህግና ሥርዓት ተከትሎ በክብረ በዓል ቀን ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ከመንግስትና ህዝባዊ ድርጅቶ ጋር በመተባበር የበዓሉን ሥነ ሥርዓት ያስከብራል፡፡ ፫. ማንኛውንም መንፈሳዊና ሥጋዊ ህግ ነክ ጉዳዮችን ይከታተላል ለሀገረ ስብከቱ አስተዳደር ጉባኤ የምክር አገልግሎት ይሰጣል እንዲሁም ሀገረ ስብከቱን ወክሎ በማናቸውም የህግ አካል ዘንድ ይከራከራል ፡፡

የሀገረ  ስብከቱ  የህግ አገልግሎት ክፍል ሥራና ኀላፊነት Read More »

የሀገረ ስብከቱ የአኃዛዊ መረጃ (ስታትስቲክስ) ክፍል ሥራና ኀላፊነት

የሀገረ ስብከቱ የአኃዛዊ መረጃ (ስታትስቲክስ) ክፍል ሥራና ኀላፊነት  ፩. በሀገረ ስብከቱ ያሉ የምዕመናን መረጃ፣መዝገበ ልደትና ጥምቀት፣መዝገበ ህያዋን፣መዝገበ ሙታን እንዲሰራባቸው ያደርጋል፡፡ ፪.በሀገረ ስብከቱ ያሉ አድባራትና አጥቢያ አብያተክርስቲያናት ማንኛውንም መረጃ ተመዝግቦ እንዲያዝ ያደርጋል፡፡ ፫. በየዓመቱ መጨረሻ በህይወት ያሉቱን የሞቱን፣ አዳዲስ የተጠመቁትን እና ወደ ሌላ ቤተ እምነት የፈለሱትን  መረጃን ፣ለአስተዳደር ጉባኤ ያቀርባል፡፡

የሀገረ ስብከቱ የአኃዛዊ መረጃ (ስታትስቲክስ) ክፍል ሥራና ኀላፊነት Read More »

Scroll to Top