የሀገረ ስብከቱ የካህናት አገልግሎት ክፍል ሥራና ኀላፊነት
፩. በሀገረ ስብከቱ ሥር ባሉ አድባራትና አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት መንፈሳዊ አገልግሎቶች ትክክለኛውን ሥነ ሥርዓት ይዘው መካሄዳቸውን ይከታታላል ይቆጣጠራል፡፡
፪. ካህናት የንሰሐ ልጆቻቸን ለመጠበቅ እንዲችሉ ከሚመለከታቸው ክፍሎች ጋር በመቀናጀት በትምህርተ ወንጌል እንዲሰለጥኑ ያደርጋል ፡፡
፫.ለክህነት የሚያበቃውን ሙያ ያወቀና ግብረ ገብነቱና መንፈሳዊ ዝንባሌው በካህናትና በምዕመናን የተመሰከረለትን እንዲሁም ወንጌልን ማስተማር የሚችል እንደ የማዕረጋቱ የዲቁናና የቅስና ማዕረግ እንዲቀበል ለሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ያቀርባል፡፡
፬. ክህነታቸው ያልታወቀና ካህን መነኩሴ ነኝ በሚሉ ላይ ቁጥጥር ያደርጋል፡፡