በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት

የሀገረ ስብከቱ ግብና ተግባራት

ሀገረ ስብከቱ የሚያከናውናቸው ተግባራት

ሀገረ ስብከቱ የሚያከናውናቸው ተግባራት የሀገረ ስብከቱን ዓላማ  ከግብ ለማድረስ በቀጣዩ አሥር ዓመት ሀገረ ስብከታችን የሚከተሉትን ተግባራት ያከናውናል፡፡ ፩. የሀገረ ስብከቱን ሙሉ ስታስቲካዊ መረጃዎችን አስባስቦና  አጠናቅሮ ይይዛል ፪.ስብከተ ወንጌል በሁሉም የሀገረ ስብከቱ ወሰን እንዲስፋፋ ያደርጋል፡፡ ፫. ሁለ ገብ የአብነት  ት/ቤቶችን በቅደም ተከተል ያቋቁማል ያደራጅማል ፬. በሀገረ ስብከቱ ክልል ውስጥ ያሉት ገጠር አብያተክርስቲያናት በተለያየ ምክንያት የተዘጉ እንዲከፈቱ […]

ሀገረ ስብከቱ የሚያከናውናቸው ተግባራት Read More »

የሀገረ ስብከቱ ጳጳስ ተግባርና ኃላፊነት

የሀገረ ስብከቱ ጳጳስ ተግባርና ኃላፊነት ተጠሪነቱ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ሆኖ፡- ፩. በዋናነት በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ክልል ውስጥ ያለችውን ቤተክርስቲያን በበላይነት ይመራል ይጠብቃል፡፡ ፪. በሀገረ ስብከት ውስጥ ለሚገኙ ካህናትና ምዕመናን መንፈሳዊ አባትና መሪ እንደመሆኑ መጠን ሃይማኖታቸውን ፣ሥርዓተ ቤተክርስቲያናቸውንና ኦርቶዶክሳዊ ትውፊታቸውን ጠብቀው እንዲኖሩ ብርቱ ጥበቃ ያደርጋል ፣መመሪያና ቡራኬ ይሰጣል፡፡ ፫. በፍትሕ መንፈሳዊ

የሀገረ ስብከቱ ጳጳስ ተግባርና ኃላፊነት Read More »

የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ሥልጣንና ተግባር

የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ሥልጣንና ተግባር ፩. የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ተጠሪነቱ ለሊቀ ጳጳሱ ይሆናል ፪. ከበላይ የሚመጡ ውሳኔዎች፣መመሪያዎችን እና የሀገረ ስብከቱ የአስተዳደር ጉባኤ ውሳኔዎችን በየደረጃው ለሚገኙት ለበታች ላሉ መዋቅሮች በወቅቱ እንዲደርሱ ያደርጋል አፈጻጸሙን ይከታተላል፡፡ ጥፋት ሲፈጸምም ከሊቀጳጳሱ መመሪያ እየተቀበለ እንደጥፋቱ መጠን የቃልና የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ይሰጣል፡፡ ፫. የሀገረ ስብከቱን አኃዛዊ መረጃዎች/ስታትስቲክስ/ የበጀት ዓመቱን የሥራ ክንውን

የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ሥልጣንና ተግባር Read More »

የሀገረ ስብከቱ ዋና ጸሐፊ ሥልጣንና ተግባር

የሀገረ ስብከቱ ዋና ጸሐፊ ሥልጣንና ተግባር ፩. የሀገረ ስብከቱን ጠቅላላ የጽህፈት ፣የሂሳብና የንብረት አጠባበቅ ሥራዎችን እንደዚሁም የልዩ ልዩ ክፍሎችን የሥራ ሂደት በቅርቡ እየተከታተለ በመቆጣጠር ይሠራል ያሠራል፡፡ ፪. የወረዳ ቤተክህነቶች ለሀገረ ስብከቱ ገቢ የሚያደርጉትን ክፍያ በወቅቱ ገቢ መሆኑን ይከታተላል፡፡ ፫. በሀገረ ስብከት ውስጥ የሚገኙ የምዕመናን አኃዛዊ መረጃዎች እንዲያዙ ያደርጋል፡፡ ፬. የሀገረ ስብከቱን የሥራ አፈጻጸምና የሒሳብ ይዘት

የሀገረ ስብከቱ ዋና ጸሐፊ ሥልጣንና ተግባር Read More »

የሀገረ ስብከቱ የስብከተ ወንጌል ክፍል ሥራና ኀላፊነት

የሀገረ ስብከቱ የስብከተ ወንጌል ክፍል ሥራና ኀላፊነት ፩. የእግዚአብሔርን ወንጌለ መንግስት መስበክና ትምህርቱንም ማስፋፋት ፪. ምዕመናን በሚረዱት እና በሚያውቁት ቋንቋ ትምህርተ ወንጌል እንዲሰጥ ተከታዮች እንዲበዙና በሰበካ ጉባኤም እንዲመዘገቡ  በማድረግ ሐዋርያዊ ተልእኮውን ይፈጽማል ፫. የስብከተ ወንጌል አገልግሎት በቅዳሴ ዕለት በክብረ በዓላት በመንፈሳዊ ጉባኤያት በሀዘንና በደስታ ስፍራዎች እንዲሰጥ ያደርጋል ተፈጻሚነቱን ይከታተላል ፬. ያለ ፈቃድ እንሰብካለን እናስተምራለን የሚሉ

የሀገረ ስብከቱ የስብከተ ወንጌል ክፍል ሥራና ኀላፊነት Read More »

የሀገረ ስብከቱ የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ ክፍል ተግባራና ኀላፊነት

የሀገረ ስብከቱ የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ ክፍል ተግባራና ኀላፊነት ፩. በሀገረ ስብከቱ ስር ባሉት አብያተ ክርስቲያናት  በቃለ ዓዋዲው መሰረት የተመረጡ የሰበካ መንፈሳዊ አስተዳደር ጉባኤያት  የአገልግሎት  ጊዜያቸው  ሲያበቃ  አዳዲስ የሰበካ መንፈሳዊ አስተዳደር ጉባኤያት እንዲመረጡ ማድረግ፤ ፪. አዲስ ለሚመረጡ የሰበካ መንፈሳዊ አስተዳደር  ጉባኤ አባላት ስለ ቃለ ዓዋዲው ስልጠና መስጠት፤ ፫. አዳዲስ በሚሰሩ አቢያተክርስቲያናት የሰበካ መንፈሳዊ አስተዳደር ጉባኤ ማቋቋም

የሀገረ ስብከቱ የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ ክፍል ተግባራና ኀላፊነት Read More »

የሀገረ ስብከቱ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ ክፍል ተግባራትና ኀላፊነት

የሀገረ ስብከቱ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ ክፍል ተግባራትና ኀላፊነት ፩.ስለ ሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች የሚወጡ ደንቦችን እና መመሪያዎችን  እየተከታተለ ለየአጥቢያ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ያስተላልፋል አፈጻጸማቸውንም ይከታተላል፤ ፪.የሰንበት ትምሀርት ቤት ባልተቋቋመባቸው አድባራት እና አጥቢያ አብያተክርስቲያናት  ያቋቁማል፤ይከታተላል፤ ፫. በተቋቋመባቸው አድባራት እና አጥቢያ አብያተክርስቲያናት ያሉ የሰንበት ትምህርት ቤቶች በቃለ ዐዋዲው መሰረት መደራጀታቸውን፤በማእከል ደረጃ የወጣውን ስርዓተ ትምህርት መተግበራቸውን ይከታተላል

የሀገረ ስብከቱ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ ክፍል ተግባራትና ኀላፊነት Read More »

የሀገረ ስብከቱ ዕቅድና ልማት ክፍል ሥራና ኃላፊነት

    የሀገረ ስብከቱ ዕቅድና ልማት ክፍል ሥራና ኃላፊነት ፩.የሀገረ ስብከቱን የአጭር የመካከለኛና የረጅም ጊዜ ዕቅድ ያወጣል አፈጻጸሙንም ለአስተዳደር ጉባኤ ያቀርባል ፪. በሀገረ ስብከቱ ሥራ የአብያተ ክርስቲያናት የይዞታ ቦታዎች ከመመሪያ ወጪ የበላይ አካል ሳይፈቅድ ለሦስተኛ ወገን እንዳይሰጡ ይቆጣጠራል ይከታተላል ፫.የሥራውን ውጤት በሚመለከት በየሦስት ወር ለአስተዳር ጉባኤ ሪፖርት ያቀርባል

የሀገረ ስብከቱ ዕቅድና ልማት ክፍል ሥራና ኃላፊነት Read More »

የሀገረ ስብከቱ የሒሳብ ክፍል ሥራና ኃላፊነት

የሀገረ ስብከቱ የሒሳብ ክፍል ሥራና ኃላፊነት ፩.የሂሳብ መዛግብትን አሟልቶ ገቢ ወጪ በህጋዊ ደረሰኝ እየሰራ በየወሩ ከወጪ ቀሪ ያለውን ያረጋግጣል በየወሩ ለጽ/ቤት መጨረሻ ሪፖርት ያቀርባል፡፡ ፪.የተበጀተውን በጀት ለታሰበለት ዓላማ መዋሉን ይከታተላል፡፡ ፫.የሒሳብ ሰነዶችንና ቼኮችን  በጥንቃቄ በመያዝ በተፈለገ ጊዜ ለኦዲት ያቀርባል፡፡ ፬.ከወረዳ እስከ አጥቢያ አብያተክርስቲያናት ድረስ በህጋዊ ደረሰኝ የሚሠራ መሆኑን ያረጋግጣል፡፡ ፭. በጀት በሚደለደልበት ጊዜ ለሚደለደለው በጀት

የሀገረ ስብከቱ የሒሳብ ክፍል ሥራና ኃላፊነት Read More »

የሀገረ  ስብከቱ  የገንዘብ  ቤት  ሥራና  ኃላፊነት

    የሀገረ  ስብከቱ  የገንዘብ  ቤት  ሥራና  ኃላፊነት ፩.ገንዘብን በህጋዊ ደረሰኝ (ካርኒ) ይቀበላል፡፡ ፪.ለማንኛውም የገንዘብ ወጪ ህጋዊ ትዕዛዝ ሲደርሰው ብቻ ክፍያ ይፈጽማል፡፡ ፫.ገቢና ወጪውን በተለየ በተዘጋጀ የገቢና የወጪ መዛግብት ላይ ይመዘግባል እንዲሁም ሂሳቡን በጥንቃቄ መዝግቦ ይይዛል፡፡ ፬.በየወሩ መጨረሻ በጠቅላላ የገባውና የወጣውን ገንዘብ ልክ ከወጪ ቀሪውን ከሂሳብ ክፍሉ መዛግባት ጋር ያመሳክራል፡፡

የሀገረ  ስብከቱ  የገንዘብ  ቤት  ሥራና  ኃላፊነት Read More »

Scroll to Top
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት