የሀገረ ስብከቱ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ ክፍል ተግባራትና ኀላፊነት
፩.ስለ ሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች የሚወጡ ደንቦችን እና መመሪያዎችን እየተከታተለ ለየአጥቢያ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ያስተላልፋል አፈጻጸማቸውንም ይከታተላል፤
፪.የሰንበት ትምሀርት ቤት ባልተቋቋመባቸው አድባራት እና አጥቢያ አብያተክርስቲያናት ያቋቁማል፤ይከታተላል፤
፫. በተቋቋመባቸው አድባራት እና አጥቢያ አብያተክርስቲያናት ያሉ የሰንበት ትምህርት ቤቶች በቃለ ዐዋዲው መሰረት መደራጀታቸውን፤በማእከል ደረጃ የወጣውን ስርዓተ ትምህርት መተግበራቸውን ይከታተላል ድጋፍም ያደርጋል፤
፬. ከሀገረ ስብከቱ ሌሎች ክፍላት ጋር በመተባበር በሰንበት ትምህርት ቤት ውስጥ ተምረው የማስተማር ብቃት ያላቸውን ተተኪ የሰንበት ትምህርት ቤት መምህራንን ያሰለጥናል ፤
፭. በየደረጃው የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት እንዲቋቋም በተወሰነው መሠረት በሀገረ ስብከት እና በወረዳ ደረጃ እንዲቋቋም ያደርጋል፤ይከታተላል፤
፮.የቤተክርስቲያኒቱን ደንብና ሥርዓት የጠበቁ መዝሙሮችን እንዲያጠኑ ያደርጋል ፤ያስደርጋል፤