የሀገረ ስብከቱ የሒሳብ ክፍል ሥራና ኃላፊነት
፩.የሂሳብ መዛግብትን አሟልቶ ገቢ ወጪ በህጋዊ ደረሰኝ እየሰራ በየወሩ ከወጪ ቀሪ ያለውን ያረጋግጣል በየወሩ ለጽ/ቤት መጨረሻ ሪፖርት ያቀርባል፡፡
፪.የተበጀተውን በጀት ለታሰበለት ዓላማ መዋሉን ይከታተላል፡፡
፫.የሒሳብ ሰነዶችንና ቼኮችን በጥንቃቄ በመያዝ በተፈለገ ጊዜ ለኦዲት ያቀርባል፡፡
፬.ከወረዳ እስከ አጥቢያ አብያተክርስቲያናት ድረስ በህጋዊ ደረሰኝ የሚሠራ መሆኑን ያረጋግጣል፡፡
፭. በጀት በሚደለደልበት ጊዜ ለሚደለደለው በጀት በቂ ገንዘብ መኖሩን ያረጋግጣል፡፡
፮.የበጀት ዓመቱ ከማለቁ ከሁለት ወራት በፊት የየወሩን ገቢ ገምግሞ የተከታዩን ዓመት በጀት በመሥራት ዝርዝርሩን ለአስተዳደር ጉባኤ ያቀርባል፡፡