የሀገረ ስብከቱ የህግ አገልግሎት ክፍል ሥራና ኀላፊነት
፩. ከበላይ አካል የሚወጡ ህጎች ደንቦች ድንጋጌዎች ውሳኔዎችና መመሪያዎች ለካህናትና ለምዕመናን እንዲያውቁትና እንዲያጠኑት ያደርጋል፡፡
፪. የሀገረ ስብከቱን ህግና ሥርዓት ተከትሎ በክብረ በዓል ቀን ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ከመንግስትና ህዝባዊ ድርጅቶ ጋር በመተባበር የበዓሉን ሥነ ሥርዓት ያስከብራል፡፡
፫. ማንኛውንም መንፈሳዊና ሥጋዊ ህግ ነክ ጉዳዮችን ይከታተላል ለሀገረ ስብከቱ አስተዳደር ጉባኤ የምክር አገልግሎት ይሰጣል እንዲሁም ሀገረ ስብከቱን ወክሎ በማናቸውም የህግ አካል ዘንድ ይከራከራል ፡፡