ኤክቱስ የካቲት 15/2018 ዓ.ም
በብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል መሪነት በዲላና ወናጎ ወረዳ ቤተ ክህነት ወደ ኦቲልቾ የስብከተ ወንጌል ኬላ በተዘጋጀው የእግር ጉዞ ላይ ተጓዦች በተለያዩ ርእሰ ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገዋል።
ውይይቱ በአምስት ምድብ ማለትም የቅዱስ ማቴዎስ፣ የቅዱስ ማርቆስ፣ የቅዱስ ሉቃስ፣ የቅዱስ ዮሐንስና የቅዱስ እስጢፋኖስ ምድብ ተከፋፍሎ ውይይት ተደርጓል።
የመጀመርያው ርእሰ ጉዳይ በገጠር አብያተ ክርስቲያናት የስብከተ ወንጌል አገልግሎትን ለማጠናከር ምን እንደሚጠበቅ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በከተማ የሚገኙ ምዕመናን ወደ ገጠሪቱ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ የአገልግሎቱ ተሳታፊ እንዲሆኑ ምን ማድረግ እንደሚገባ በተጨማሪም ምዕመናንን መንፈሳዊ ዕውቀት እንዳይኖራቸው የሚያደርጋቸው ተግዳሮቶች ምን እንደሆኑ በሰፊው በመወያየት የተለያዩ ምክረ ሃሳቦች ቀርበዋል።

Pingback: cefixime