በአርሲ ለተገደሉ ምዕመናን ጸሎተ ምሕላ ተደረገ!!
በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት በአንዲዳ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ዓመታዊው የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጥንተ ስቅለቱ እንደተከበረ ከዚህ በፊት በነበረ ዘገባ መግለጻችን ይታወቃል። በመርሃግብሩ በቅርቡ በኦሮሚያ ክልል በአርሲ ዞን በኦርቶዶክሳውያን ላይ በተደረገው ጥቃት በብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል መመሪያ ሰጪነት እግዚአብሔር አምላክ የሞቱትን ነፍስ እንዲምርና በሀገሪቱ ላይ የመጣውን መቅሰፍት በምሕረቱ እንዲመልስ ጸሎተ ምሕላ ተደርጓል። በተጨማሪም ብፁዕነታቸው በአከባቢው የሚገኙ የሚመለከታቸው አካላት የአከባቢውን ሰላም ማስከበር ቀዳሚ ተግባራቸው እንደሆነ በአጽንዖት ገልጸዋል።
በአርሲ ለተገደሉ ምዕመናን ጸሎተ ምሕላ ተደረገ!! Read More »