የሀገረ ስብከቱ የስብከተ ወንጌል ክፍል ሥራና ኀላፊነት
፩. የእግዚአብሔርን ወንጌለ መንግስት መስበክና ትምህርቱንም ማስፋፋት
፪. ምዕመናን በሚረዱት እና በሚያውቁት ቋንቋ ትምህርተ ወንጌል እንዲሰጥ ተከታዮች እንዲበዙና በሰበካ ጉባኤም እንዲመዘገቡ በማድረግ ሐዋርያዊ ተልእኮውን ይፈጽማል
፫. የስብከተ ወንጌል አገልግሎት በቅዳሴ ዕለት በክብረ በዓላት በመንፈሳዊ ጉባኤያት በሀዘንና በደስታ ስፍራዎች እንዲሰጥ ያደርጋል ተፈጻሚነቱን ይከታተላል
፬. ያለ ፈቃድ እንሰብካለን እናስተምራለን የሚሉ ግለሰቦችን መቆጣጠር ወደ ህጋዊ መስመር እንዲመጡ ማድረግ
፭. በሀገረ ስብከቱ የሚገኙ ሰባኪያነ ወንጌልን ማብቃት ማሰልጠን ዘመኑን የዋጀ አገልግሎት እንዲሰጡ ማድረግ እና በበጎ ፈቃድ የሚያገለግሉ ሰባኪያነ ወንጌልን ማስልጠን ህጋዊ ፈቃድ እንዲያገኙ ማድረግና መከታተል
፮.የስብከት ኬላዎችን በማቋቋም የስብከተ ወንጌል አገልግሎት ምዕመናን በሚሰሙት ቋንቋ እንዲሰበክ ያደርጋል፡፡
፯. ለምዕመናን፣ለሰንበት ት/ቤት አባላትና ለካህናት ምቹ ሁኔታዎችን በማመቻቸት የትምህርተ ሃይማኖት ኮርሶችን ይሰጣል እንዲሰጥ ያደርጋል፡፡
፰. ከቤተክርስቲያን እውቅና ውጪ የሆኑ የህትመት የድምጽና የምስል ውጤቶችን እንዳይሰራጩ ይቆጣጠራል ተፈጻሚነቱን ይከታተላል፡፡ እንዲሁም የተፈቀደላቸው ለምዕመናን እንዲሰራጩ ያደርጋል፡፡