የሀገረ ስብከቱ የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ ክፍል ተግባራና ኀላፊነት
፩. በሀገረ ስብከቱ ስር ባሉት አብያተ ክርስቲያናት በቃለ ዓዋዲው መሰረት የተመረጡ የሰበካ መንፈሳዊ አስተዳደር ጉባኤያት የአገልግሎት ጊዜያቸው ሲያበቃ አዳዲስ የሰበካ መንፈሳዊ አስተዳደር ጉባኤያት እንዲመረጡ ማድረግ፤
፪. አዲስ ለሚመረጡ የሰበካ መንፈሳዊ አስተዳደር ጉባኤ አባላት ስለ ቃለ ዓዋዲው ስልጠና መስጠት፤
፫. አዳዲስ በሚሰሩ አቢያተክርስቲያናት የሰበካ መንፈሳዊ አስተዳደር ጉባኤ ማቋቋም ፤
፬. በሀገረ ስብከቱ ስር ባሉ አብያተ ክርስቲያናት በቃለ ዓዋዲው መሰረት የተመረጡ የሰበካ መንፈሳዊ አስተዳደር ጉባኤያት የሚጠበቅባቸውን ተግባራት እንዲፈጽሙ ማገዝ እና መከታተል፤
፭. ወቅታዊ የቤተክርስቲያን መረጃ በአጥቢያ፤በወረዳ ቤተክህነት እና በሀገረ ስብከት እንዲመዘገብ እና እንዲደራጅ ማድረግ፤