በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት

የሀገረ ስብከቱ የመንፈሳዊ ትምህርት ክፍል ሥራና ኀላፊነት

፩.በሀገረ ስብከቱ በሚገኙ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት መንፈሳዊና ዘመናዊ ት/ቤት እንዲቋቋም ያደርጋል እንዲሁም ለተማሪዎችም የሚያስፈልገውን በጀት እንዲመደብ የሚመለከታቸውን ሁሉ ያስተባብራል፡፡

፪.የትምህርት መስጫ ቦታዎች አመቺ እንዲሆኑና መምህራን ጉባኤያቸውን ሳይፈቱ እንዲያስተምሩ ያደርጋል፡፡

፫. ቤተ መጻሕፍት እንዲያቋቁሙና ካህናት ዲያቆናት የሰንበት ት/ቤት ተማሪዎች ተገኝተው እንዲያነቡ አስፈላጊው ሁሉ እንዲፈጸም ያደርጋል፡፡

፬. ህጻናት በሥነ ምግባርና በሃይማኖት ተኮትኩተው እንዲያድጉ ያደርጋል፡፡ ፭. የመማር የማስተማር ሂደት በተሳለጠ መልኩ በቅርበት ሆኖ ይቆጣጠራል፡፡

Scroll to Top
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት