በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት

የሀገረ ስብከቱ ዋና ጸሐፊ ሥልጣንና ተግባር

፩. የሀገረ ስብከቱን ጠቅላላ የጽህፈት ፣የሂሳብና የንብረት አጠባበቅ ሥራዎችን እንደዚሁም የልዩ ልዩ ክፍሎችን የሥራ ሂደት በቅርቡ እየተከታተለ በመቆጣጠር ይሠራል ያሠራል፡፡

፪. የወረዳ ቤተክህነቶች ለሀገረ ስብከቱ ገቢ የሚያደርጉትን ክፍያ በወቅቱ ገቢ መሆኑን ይከታተላል፡፡

፫. በሀገረ ስብከት ውስጥ የሚገኙ የምዕመናን አኃዛዊ መረጃዎች እንዲያዙ ያደርጋል፡፡

፬. የሀገረ ስብከቱን የሥራ አፈጻጸምና የሒሳብ ይዘት መግለጫ ለመጭው ዓመት ከሚፈቅደው ዓመታዊ የገንዘብ ድልድል (በጀት) ጋር አዘጋጅቶ በሥራ አስኪያጁ አማካኝነት ለአስተዳደር ጉባኤ ያቀርባል፡፡

፭.የሀገረ ስብከቱን የልዩ ልዩ የሥራ ክፍሎች የሚቀርብለትን የሥራ ክንውን እንዲሁም አኃዛዊ መረጃዎችን በማጠቃለል በየሦስት ወሩ ለአስተዳዳር ጉባኤ ሪፖርት ያቀርባል፡፡

Scroll to Top