የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ሥልጣንና ተግባር
፩. የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ተጠሪነቱ ለሊቀ ጳጳሱ ይሆናል
፪. ከበላይ የሚመጡ ውሳኔዎች፣መመሪያዎችን እና የሀገረ ስብከቱ የአስተዳደር ጉባኤ ውሳኔዎችን በየደረጃው ለሚገኙት ለበታች ላሉ መዋቅሮች በወቅቱ እንዲደርሱ ያደርጋል አፈጻጸሙን ይከታተላል፡፡ ጥፋት ሲፈጸምም ከሊቀጳጳሱ መመሪያ እየተቀበለ እንደጥፋቱ መጠን የቃልና የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ይሰጣል፡፡
፫. የሀገረ ስብከቱን አኃዛዊ መረጃዎች/ስታትስቲክስ/ የበጀት ዓመቱን የሥራ ክንውን እና የፋይናንስ ሪፖርት ለመንበረ ጵጵስናው ሰበካ መንፈሳዊ አስተዳደር ጉባኤ በወቅቱ ያቀርባል፡፡