በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት

ታሪካዊ ቦታዎች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን

  1. የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተመዘክር፤
  2. የገነተ ጽጌ ቅ/ጊዮርጊስ ቤ/ክ ቤተመዘክር፤
  3. የርዕስ አድባራት እንጦጦ መንበረ ፀሐይ ማርያም ቤ/ክ ቤተመዘክር፤
  4. የታዕካ ነገስት በዓታ ለማርያም ቤ/ክ ቤተመዘክር ወዘተ መጥቀስ ይቻላል

የቤተመዘክሮቹ ዋና ዓላማ

  • ሃይማኖታዊና ታሪካዊ የሆኑትን የቤተክርስቲያን ቅርሶች በሙዚየም ውስጥ በማደራጀት በልዩ ጥበቃና እንክብካቤ ይዞ ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገር ጐብኝዎች በማስጐብኘት የቤተክርስቲያኒቱን ታሪካዊ ገጽታ በዓለም ደረጃ እንዲታወቅ ማድረግ፣
  • እነዚሁ አስደናቂ ታሪኮችንና ሃይማኖታዊ ቅርሶችን በጥንቃቄ ጠብቆ በመያዝ ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍ ነው፡፡

ከእነዚህም መካከል ለአብነት ያህል በየክፍላቸው መድበን እንደሚከተለው አቅርበናል፡፡

  1. 1ኛ. ከታሪካዊ ቅርሶች
    • የነገሠታቱ የቤተ ክርስቲያን ውስጥ የክብር ዙፋኖች፣
    • የነገሥታቱ የአርበኝነት አልባሳት፣
    • በሞዛይክ ቅርፅ የተዘጋጀ የአፄ ኃይለ ሥላሴ ምስል (ፖርትሬት) እና ሌሎችም፣
  2. 2ኛ. ከሃይማኖታዊ ቅርሶች
    • በተለያየ ዲዛይን የተሠሩ መስቀሎች፣
    • ልዩ ልዩ ጽዋዎችና ጻሕሎች ከነእርፈ መስቀሎታቸው፣
    • የተለያዩ ወርቀ ዘቦና የብር ጥልፍ (ሙካሽ) ሥራ ካባዎችና ድባብ ጥላዎች፣
    • የተለያዩ የብራና ቅዱሳት መጻሕፍት ገበታቸው በወርቅና በብር የተለበጡ ጭምር፣
    • ከዕንቀ፣ ከብርና ከሞዛይክ የተሠሩ ቅዱሳት ሥዕላት፣ ሥነ-ስቅለትና የመሳሰሉት ይገኛሉ፣
      ሰጭዎቹም ዘርዝር
    • ከብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትና ከሌሎችም አባቶች፣
    • ከዳግማዊ ዐፄ ምኒልክ፣
    • ከቀ አፄ ኃይለ ሥላሴ፣
    • ከንግሥት ዘውዲቱ፣
    • ከእቴጌ ጣይቱ፣
    • ከእቴጌ መነን፣
    • ከልዑላትና ከልዕልቶቹ፣
    • ከቀድሞ ቤተ መነግሥት ባለሥልጣናት፣
    • ከበጎ አድራጊ ክርስቲያኖች፣
    • ከአኀት አብያተ ክርስቲያናትና ከሌላም
Scroll to Top
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት