በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት

“ሰፍሐ እደዊሁ ለሕማም – እጆቹን ለሕማም ዘረጋ”  ቅዳሴ ሐዋርያት

እንኳን ለመድኃኔዓለም ጥንተ ስቅለት በዓል አደረሰን አደረሳችሁ!

Your Attractive Heading

Your Attractive Heading

የዛሬው በዓላችንን የምናከብርበት ምክንያት እግዚአብሔር ለሰው ልጅ ያለውን ጥልቅ ፍቅር የገለጠው አንድያ ልጁን ወደ ምድር ልኮ በተቀበላቸው ጸዋትወ መከራን በማሰብ ነው። የመጨረሻ ፍቅሩንም ያሳየው በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ሞቶ ነው።

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለምን መከራን ተቀበለ?

እግዚአብሔር የሰውን ልጅ ከመፍጠሩ በፊት ለሰው የሚያስፈልገውን እንዳይቸገር ሁሉን አመቻችቶ (አዘጋጅቶ) በስድስተኛው ቀን ዐርብ ዕለት በእርሱ መልክና አርአያ ፈጠረው በምድርም ላይ ለሚኖሩ ፍጥረታት ገዢ አድርጎ ከጎኑም አጥንትን ወስዶ ሔዋንን ፈጠረለት። አዳምና ሔዋን በገነት መካከል ያሉትን ፍሬዎች እንዲበሉ ፈቀደላቸው ነገር ግን ዕፀ በለስ የተባለችውን ፍሬ እንዳይበሉ አዘዛቸው ከዚህች ፍሬ ብትበሉ የሞት ሞትን እንደሚሞቱ አስጠነቀቃቸው።

አዳምና ሔዋን ግን የእግዚአብሔርን ትዕዛዝ አክብረው መኖር የቻሉት ለሰባት ዓመታት ብቻ ነበር ሰይጣን ዲያብሎስ በእባብ ገላ አድሮ ወደሔዋን በመሄድ ከንቱ የሆነ ውዳሴን ለሔዋን በማቅረብ “ዕፀ በለሱን አትብሉ ያላችሁ እግዚአብሔር አምላክ እንዳትሆኑ ብሎ ነው ስለዚህ ከዕፀ በለሱ ብትበሉ አምላክ ትሆናላችሁ” ብሎ ሔዋንን ዕፀ በለሱን እንድትበላ የሐሰት ስብከትን ሰበካት ሔዋንም ቀጥፋ የዲያብሎስን ምክር ሰምታ ከአዳም ጋር በሉ። በበሉም ጊዜ ጸጋቸው ተገፈፈ ፍርሃትም ወደቀባቸው እግዚአብሔርም ከእነርሱ ተለየ
አዳምና ሔዋንም በእግረ አጋንት በኃጢአት ወድቀው ከክብር ተዋርደው በለስን በልተው ሞትን ሸምተው ለብዙ ዘመናት በጨለማ፣በፍርሃት፣የብርሃን ጸጋቸው ተገፎ በሐዘን ውስጥ ስንሰቃዩ እግዚአብሔርም ተመልክቶ   ተገለጠላቸውና አምስት ቀን ተኩል ሲፈጸም ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለው ብሎ ቃል ኪዳን ለአዳም ገባለት።
በዚህም ጌታችን ሞታችንን ወስዶ ሕይወት ሊሰጠን መድኃኒት ልጁን ላከልን። “ፈነወ ለነ መዝራእቶ ልዑለ – ልዑል ክንዱን ሰደደልን” እንዳለ ሶርያዊው ቅዱስ ኤፍሬም
በተጨማሪም ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ “እኛም አይተናል አባትም ልጁን የዓለም መድኃኒት ሊሆን እንደላከው እንመሰክራለን” 1ኛ ዮሐ 4፥14

በዚሁ መሠረት ከሦስቱ አካል አንዱ ወልድ በተለየ አካሉ ከሰማየ ሰማያት ወረደ ተወለደ ይኸውም ለአዳም ልጆች በሙሉ ለበደልነው፣ ለወንጀለኞች፣ ሕጉን ለጣስነው፣ በጨለማ ውስጥ ላለነው ፣ በሞተ ሥጋ ሞተ ነፍስ በርደተ መቃብር ርደተ ሲዖል እንድንወርድ ተፈርዶብን ለነበረው ፣ በእግረ ዲያብሎስ ስንረገጥ ለነበርነው እና ምንም የሚወደድ ማንነት የሌለን ስንሆን “እግዚአብሔር አንዲያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና።ዮሐ 3፥16

  ለኛ ሲል ምን ምን መከራን ተቀበለ?

“የወልድን መከራውን የሚናገር ምን አፍ ነው? ምን ከንፈር ነው? ምን አንደበት ነው? የፍቁር የጌታ ሕማማት በተነገረ ጊዜ ልብ ይለያያል ሕሊናም ይመታል ነፍስም ትንቀጠቀጣለች ሥጋም ይደክማል”

1ኛ ከሊቶስትራ እስከ ቀራንዮ ከጲላጦስ አደባባይ እስከ ቀያፋ ጊቢ በአይሁድ በሊቃነ ካሕናት እጅ ተሰቃየ፣ ስድስት ሺህ ስድስት መቶ ስልሳ ስድስት ጊዜ በጅራፍ ተገረፈ፣ አንድ መቶ ሃያ ጊዜ በጥፊ ተመታ፣ ሰማንያ ጊዜ ጺሙን ነጩት፣ ሰባ ሁለት ጊዜ አፉን በጡጫ መቱት፣ ሦስት መቶ የሚሆኑ ረዣዥም የእሾህ አክሊል በራሱ ደፉበት፣ ምራቅ ተፉበት፣ መስቀል ተሸክሞ እየወደቀ እየተነሳ ተሰቃየ።
“እርሱ ግን ስለመተላለፋችን ቆሰለ ስለበደላችንም ደቀቀ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ በእርሱም ቁስል እኛ ተፈወስን።” ኢሳ 53 ፥7

እንዲሁም ጌታችን ስድስት ሰዓት ሲሆን አዳምና ሔዋን አትብሉ የተባሉትን ዕፀ በለስ የበሉት በዚህ ሰዓት ነበረና ይህንን ለመካስ በስድስት ሰዓት ተሰቀለ።

ጌታችን በመስቀል እያለ ተአምራት ተፈጽመዋል በሰማይና በምድር

1ኛ ጸሐይ ጨለመ
2ኛ ጨረቃ ደም ለበሰች
3ኛ ከዋክብት ረገፉ

        # በምድር
1ኛ መቃብራት ተከፍተው ከ500 በላይ የሚሆኑ ሙታን ተነሱ
2ኛ ድንጋዮች ተሰነጣጠቁ
3ኛ የቤተ መቅደስ መጋረጃ ለ2 ተከፈለ
4ኛ ዓለም ሁሉ ጨለማ ሆነ

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ እያለ

13ቱን ህማማተ መስቀል ተቀብሏል።

ጌታችን በመስቀል ላይ እያለ “ተጠማሁ “
ሲል አንጀት የሚበጥስ ሀሞትና ከርቤ ቀላቅለው አጠጡት ሁሉን የሚያጠግበውን አጠጥቶ የሚያረካውን ተጠማሁ አለ።

40 ቀንና 40ሌሊት በጌቴሴማኒ  የጾመ ጌታ በአይሁድ እጅ 18 ሰዓታት ሳይሞላ ተጠማሁ ያላቸው ለምን ይሆን?

ፍቅርን ሲገልጽ ነው አይሁድ ከታላቁ እስከ ታናሹ ድረስ በጠላትነት ተነስተውበታልና ለዚህም ነው ተጠማሁ ፍቅር ተራብኩ ሲል ነው።

     ይህን ፍቅር የሆነውን ጌታ እስከመስቀሉ ያልተለዩ ሁለቱ ብቻ ነበሩ

1ኛ ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ የሚደርስበትን መከራ እስከ ቀራንዮ እየተከተለ መከራውን ፣ስቃዩን፣ መንገላታቱን ግርፋቱን አይሁድን ሳይፈራ ያይ ነበር ወንጌላዊው ቅ/ዮሐንስ ጌታ ይወደው የተባለው ቁጽረ ገጽ (ፊቱ በሐዘን) የሞላ የተባለው ለዚህም ነው በመጨረሻም በመስቀል እያለ እናቱን እነኋት እናትህ ብሎ በአደራነት የሰጠው
2ኛ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት እርሷም የአይሁድን ዛቻ ዱላ ሳትፈራ እስከ ቀራንዮ የተከተለች በውስጧ እያለቀሰች ያ ሁሉ ስቃይ ሲደርስበት መጨረሻውን ሳላይ የትም አልሄድም ብላ መስቀሉ ስር የተገኘች

ለመዳናችን ምክንያት የሆነች ንጽሕት፣ቅድስት፣ድንግል ለሁላችን የተሰጠች እናት ናት።

   ስለዚህ የተከፈለልንን ውለታ በማሰብ በሕይወት ልንኖር ይገባል።

1ኛ በፍቅር ልንመላለስ ይገባል።

        እኔ እንደወደድኳችሁ እርስ በእርሳችሁ ትዋደዱ ዘንድ ትዕዛዜ ይህች ናት    ዮሐ 15፥12
ጠላቶቹ ሳለን ከወደደን
     1ኛ 4፥16 እኛም እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን ፍቅር አውቀናል አምነንማል እግዚአብሔር ፍቅር ነው በፍቅርም የሚኖር በእግዚአብሔር ይኖራል እግዚአብሔርም በእርሱ ይኖራል።
2ኛ በትህትና ሕይወት ልንኖር ይገባል
እርሱን ሲንቁት አልናቃቸውም ሲታበዩበት በትህትና ያያቸው ነበር።
    ሉቃ 23፥34    አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው አለ
እኛም ሰዎች ሲንቁን ሲታበዩብን በዝምታ በፍቅር ልናሳልፍ ይገባል።

3ኛ በትዕግስት ፦ እርሱ ሲሰድቡት  አልተሳደበም፣ በፈጠራቸው ፍጥረታት ምራቅ ተተፋበት ምንም መልስ አይሰጣቸውም ነበር በትዕግስት ይመለከታቸው ነበር እንጂ
           2ጴጥ 3፥15 የጌታችንም ትዕግስት መዳናችሁ እንደሆነ ቁጠሩ
4ኛ ሮሜ6፥5       ሞቱንም በሚመስል ሞት ከእርሱ  ጋር ከተባበርን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ደግሞ ከእርሱ ጋር እንተባበራለን
                     
ጌታችን ከቤተልሔም ጀምሮ ብርዱ፣ የግብጽ ስደቱ፣ረሃቡ ጥማቱ ከሐሙስ ማታ 3፡00 እስከ ዐርብ 9፡00 የተቀበላቸው መከራዎች ለሰው ልጅ ነው
እኛም የእርሱ እውነተኛ ደቀ መዝሙር ስንሆን የሚደርስብን ልዩ ልዩ መከራ አለ ነገር ግን የኛ አምላክ በመስቀል ተሰቅሎ በአዲስ መቃብር ተቀብሮ መቃብር ሊይዘው ሳይችል መግነዝ ፍቱልኝ መቃብር ክፈቱልኝ ሳይል በራሱ ኃይልና ሥልጣን ሞትን ድል አድርጎ አሸንፎ ተነስቷል እኛም በእምነት ጸንተን ንስሐ ገብተን በመስቀል ላይ የቆረሰውን ቅዱስ ሥጋውን በልተን ደሙን ጠጥተን መንግስቱን እንድንወርስ ከእርሱ ጋር ለዘለዓለም እንድንኖር አምላካችን ይርዳን።
       
ስብሐት ለእግዚአብሔር!

መምህር በየነ ክፍሌ
የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት
ቁጥጥርና የምግባረ ሰናይ ክፍል ኃላፊ

Scroll to Top